አርበኛ ሁን ካህን!

መጣፉ ያዝዛል እንድትገጥም ሰይጣንን፣
ተሕዝብ እንድትነቅለው ነግንገህ ቁንጮውን፣
ሳትውል ሳታድር አርበኛ ሁን ካህን!

ፈለግን ተከል የጴጥሮስ አድማሱን፣
ክፉ አምስት ዘመን ዳግም ሲመጣብን፡፡

እንኳንና ሕዝቡ እንዳትገዛ ምድር፣
በግዝት መሀላ በጸሎት ውል እሰር፣
ጭራቅ አገር ወሮ ተኝተህ ላታድር፡፡

ከበሮ ደልቀህ እምቢልታውን ነፍተህ፣
ፀናጽል አፋጭተህ መቋሚያህን ሰብቀህ፣
አዋጅ! አዋጅ! ብለህ ሞረሽ ክተት ጠርተህ፣
ክላ ዲያብሎስ በል ተአገር ሳያጠፋህ!

ሰሜን እስተ ደቡብ ቀጥ ብለህ ቆመህ፣
ተምስራቅ ምዕራብም አግድም ተያይዘህ፣
የወልድን ምልክት መስቀል በአንገት አስረህ፣
እንደ ጉም አብነው ሳጥናኤልን ገፈህ፣
ተመልካች አትሁን ሲጨስ ሲነድ ሕዝብህ፡፡

ዜማውን አዚመህ ቅኔን ተቀኝተህ፣
ጸበልን እረጭተህ በመስቀል ደልዘህ፣
አስወጣ ዲያብሎስ ዛሩን አስጎርተህ፡፡

እግዜር ተሳጥናኤል እንዳልታረቀ አውቀህ፣
ማተብ ታላሰረ ሽምግልና አቁመህ፣
ቃል አባይ ከሀዲን ዳግም ማመን ትተህ፣
መንን ወደ ጫቃ ጥራኝ ፋኖ ብለህ፡፡

ለምተዋት ዓለም ነገ ለማትኖር፣
ሥጋህ አሸንፎ ነፍስ አትግባ ሲኦል፡፡

እግዜርና ታሪክ ጥሪ ሲያቀርቡልህ፣
አደጋ ሲወድቁ አገርና ሕዝብህ፣
እንድታድናቸው በሥጋ በደምህ፣
አርበኛ ሁን ካሀን እንደ ቅድመ አያትህ፡፡

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)
ታህሳስ ሁለት ሺ አስራ ስድስት ዓ.ም.

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሸገርና ምርጫ፣ ባልደራስና ፊርማ (አሁንገና ዓለማየሁ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share