ይድረስ ለአርበኛ ዘመነ ካሤና መሰል “ታጋዮች”ና ታጋዮች!

ብሥራት ደረሰ

ምንም ነገር የመጻፍ ፍላጎት የለኝም፡፡ ጊዜው ሀገራችን ልትወለድ ምጥ የበዛት በመሆኑ ከመጻፍ ይልቅ የነገሮችን አካሄድ በጥሞና የመከታተያ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ላለፉት አራት አሠርት ዓመታት ገደማ ብዙ ብለናል፡፡ አሁን በክፉም ሆነ በደግ የገነኑ ሰዎች ወደ መድረክ ከመዝለቃቸው ብዙ ዓመታት አስቀድመን ስለሀገራችን መፃዒ ሁኔታ ሣይቀር ጥቂት የማንባል ወገኖች ብዙ ለፍልፈናል፡፡ ከጮህንበት ውስጥ አብዛኛው በተግባር ታይቶ የሀገር ትንሣኤው ብቻ ይቀራል፡፡ ይህ ነባራዊ ክስተት ደግሞ በቅርቡ እውን ይሆናል፡፡ የሀገር ጠላቶችም ግብዓተ መሬታቸው ይፈጸማል – ዓለም እያዬ!!

በዚህን አስቸጋሪ ወቅት ነው እንግዲህ ዝም ማለት ያላስቻለኝ ነገር የተፈጠረው፡፡ ነገሩ ትናንት ማታ ነው፡፡ አንድ ሚዲያ ስከታተለል ታጋይ አርበኛ ዘመነ ካሤ ሲናገር ሰማሁና ሙሉውን አዳመጥኩት፡፡ ጥሩ ንግግር ነው፡፡ ነገር ግን የእስክንድርን ስም ሲያነሳ “ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ” ብሎ እንደቀላል ነገር ሲናገር ስሜቴ ተረበሸ፡፡ እኔ ዘመነን ብሆን “አርበኛ ፋኖ እስክንድር ነጋ” እል ነበር – “አክቲቪስት፣ ጋዜጠኛ፣ ታላቁ እስክንድር…” የሚለው ቀርቶበት አሁን በተሠማራበት የትግል መስመሩ ቢጠራ ማንም አይጎዳም፤ መከባር ደግሞ ከቤት ይጀምራል፡፡ “ከአነጋገር ይፈረዳል፣ ከአያያዝ ይቀደዳል” እንዲሉ መላ ሕይወቱን ለሀገሩ የገበረን ሰው በዚህ መልክ አሳንሶ መጥራት ለኔ የሸተተኝ ነገር አለ፡፡ እርግጥ ነው እስኬው ጋዜጠኛ ነበር፡፡ አሁን ግን አይደለም፡፡ አሁን ሌላ ነው፡፡ የፋኖ አደራጅና ትልቅ ሥራ በመሥራት ላይ የሚገኝ ሁለመናውን ለኢትዮጵያ ትንሣኤ የሰጠ እንደማንኛውም የፋኖ አባል ሁሉ ውድ ልጃችን ነው፡፡ ጋዜጠኛ መባል ከነበረበት በፊት ነው፡፡ አሁን ግን ይህን ዕንቁ ሰው ወደ ጋዜጠኝነት ሙያ መመለስ ውስጠ ወይራው አልገባኝም፡፡ ለምን?

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከአማራ ቆዳ በተሠራ ከበሮ: ጭፋሮ !! (አሥራደው ከፈረንሳይ)

የኢትዮጵያ ትንሣኤ ብዙ አሣር እንዳለበት ይገባኛል፡፡ በአንድ ጎራ ባሉ ወገኖች ግን ይህ አሣር መቀነስ አለበት፡፡ ካለፈው ተሞክሯችን መማር አለብን፡፡ እዬዬም ሲደላ ነው፡፡ አማራንና ኢትዮጵያን ክፉኛ እየጎዳት ያለው ይሄ የኢጎ ጉዳይ ነው – ራስን ከፍ አድርጎ የመገመትና ለሌሎች ዝቅተኛ ግምት የመስጠት አባዜ ክፉኛ እያወከን ይገኛል፡፡ ብዙ ሚሊዮን አማራን በነፍሰ ሥጋው እየተጫወተበት ያለው አስጠሊታ ነገር የድል ሽሚያና የሥልጣን ፍቅር ነው፡፡ በዚህ ረገድ አማራ አልታደለም፡፡ ብዛቱና ዕውቀት ጥበቡ እያለው በትንሾች እንደክርስቶስ የሚወገረው የራሱ ልጆች አልስማማ ብለው እርስ በርስ ስለሚናናቁና እንደጅብ ስለሚዘራጠጡ ነው፡፡ መጥፎ ጠባይ፡፡

አራት ኪሎ የሚችለው አንድ ሰው ነው፡፡ 15 ሚሊዮን ፋኖ ቢኖር ሁሉም አራት ኪሎ አይገባም፡፡ 100 ሽህ የፋኖ መሪ ቢኖር ሁሉም ያቺን የምታሳብድና የምታቃዥ ወንበር አይዝም፡፡ በጊዜ የጮኸ ጅብ አያሳድረኝም የሚባለው አለነገር አይደለም፡፡ በረሃ እያለ በአልደፈርም ባይት የሚኩነሰነስና በብዙ አጃ የሚቆነን ሰው አራት ኪሎ ቢገባ ምን ሊያሳየን እንደሚችል ከወዲሁ ይታወቃልና ከዚህ ዓይነቱ መጥፎ ጠባይ እንድትርቁ ምክራችን የሚያስልጋችሁ ወገኖቻችንን ከአሁኑ እንመክራለን፡፡ ሰው ዐይን ውስጥ አትግቡ፡፡ ትሁት ሁኑ፡፡ ትኅትናችሁ ወደላይ ያውጣችሁ፡፡ ላዩን ከፈለጋሁ ደግሞ ታቹን ምረጡ፡፡

አሁን ደግሞ የወቅቱ ትኩረት የወንበር ጉዳይ ሳይሆን የኅልውና ጉዳይ ነው፡፡ መጀመሪያ የመቀመጫየን ብላለች ዝንጀሮ፡፡ አማራ በመሆኑ ምክንያት ተወልዶ እንዳያድግ ጽንስ ከሆድ እየተቀደደ በቢላ በሚቀረደድበት ሰዓት፣ አማራ ቆሞ ብቻ ሳይሆን ታሞ ተኝቶም መኖር እንዳይችል ከያለበት በኦሮሞ እየታደነ በሚታጨድበት ወቅት፣ የአማራ ምድር የሚባለው ሳይቀር በኦህዲድ መከላከያ ተወርሮ ዜጎች ቀን ከሌት እየታጨዱ በሚገኙበት ዘመን፣ አዲስ አበባ መግባት ለአማራ ህልም በሆነበት ሁኔታ፣ የአማራ ቤትና ሰውነት በተረኛ ዘረኞች እየፈራረሰና አማራ ሎተሪ አዙሮ ወይም ዘበኝነት ተቀጥሮ እንኳን መኖር ባልተፈቀደለት ወቅት… እንዲህ ዓይነት ቅንጡ የሥልጣን መራኮት ከአሁኑ ሲታይ በርግጥም የአማራው መረገም ሥር የሰደደ እንደሆነ መረዳት አይከብድም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  አዲስ ጉዳይ መጽሔት፡ “የመጀመሪያው ድምፅ” ዕድሎቹና ፈተናዎቹ

ስለዚህ እባክህን ዘመነ ሆይ! እባችሁን ዘመነዎች ሆይ! መጀመሪያ በየቀኑ ለምንታረደው ዜጎች ቅድሚያ ስጡ፡፡ የሥልጣን አራራውና ሽኩቻው ይደርሳል፡፡ ሀገር ሲኖር ለሚደርስ ነገር ጠላቶች እስኪስቁባችሁ ሳይቀር አትወዛገቡ፡፡ አማራን አማራ እንዲህ እየጠለፈው የትም አይደረስም፡፡

ሁሉም ነገር እንደሚጠራ አውቃለሁ፡፡ አማራዊነት እንደሚያሸንፍ ዘመነ ጫካ ከመግባቱ በፊት ብዙ ተጮሆበታል፡፡ የሚያበሳጨኝ ግን በዚህን ወቅት እንኳን ከብአዴን ተምሮ አማራነትንና ኢትዮጵዊነትን ከማስቀደም ይልቅ የግል የሥልጣንና የጥቅም ፍላጎትን በማስቀደም ለትዝብት በሚዳርግ ሁኔታ የሚሠራው የጭቡ ሥራ ነው፡፡ ይገርማል፡፡ ፋኖን እግዚአብሔር ከውስጥም ከውጭም ይጠብቀው፡፡

በመጨረሻም እንዲህ ልበልና ልጨርስ፡፡ በምንም ምክንያት ይሁን በምን አማራን ሊከፋፍልና ለኦሮሙማው የዘር ፍጂት ዳርጎ ሁሉንም አማራ ተራ በተራ ለማስፈጀት የሚንቀሳቀስ ሆዳም አማራ የእነፕሮፌሰር አሥራትና የእነአሣምነው ጽጌ ዐፅም እሾህ ሆኖ ይውጋው፡፡ የአማራን ኅልውና ለግል ጥቅም የሚሸጥ አስመሳይና የውስጥ ባንዳ ዘር አይውጣለት፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ፡፡

 

10 Comments

  1. አስተያየቱ እንደ አስተያየት መልካም ነው።
    ጋዘጠኛ እስክንድር ቢባልም ምንነቱና ማንነቱ ግልፅና ግልፅ ነውና ብዙም ስህተትነት ያለው አይመስለኝም። ምናልባትም ይህ የሙያ ስምን እርሱ ራሱ የመረጠውም ሊሆን ይችላልና ለማወቅ መጠየቅና ከዚህም ተነስቶ ሊሆን ይገባዋል ወይም መሆን አለበት የሚል ምክንያታዊ አስተያየት ለድርጅቱም ሆነ ለእስክንድር መለገስ የሚሻል ይመስለኛል።

    በውል ባላወናቃቸው ምክንያቶች የሚባሉ የማእረግም ሆነ ሌላ ስያሚዎች ለምንና እንዴት እንደተባሉ በጥያቄ መልክ ከማወቅና አስተያየት ከመስጠት ይልቅ የተጋነነ የሚመስል አስተያየት መስጠት ለወሬኞችና ለጭራቃዊው ገዥ ቡድን ተቀጣሪ የፕሮፓጋንዳ አተላ ( ግብስብስ) ነው የሚመቸውና …።

    • ለፅሁፉ አስተያይት የሰጠኸው አኪል ሚዛናዊ ነህ?
      ፅሁፉ የሚጭረው ነገር ያለ ይመስላል!?
      ሆን ተብሎም ለታጋዮች ያለንን አዎንታዊ ሀሳብና ድጋፍም ፖዝ ለማድረግ ይመስላላ!?
      እንጅማ እስክንድር ጋዜጠኛ ቀመሆኑ ከዘመነ ይልቅ በዓለም ደረጃ በስፋት ይታወቅበት አይደል።

  2. Well, the point which raises the need to control if not to avoid the very ugly internal political power struggle by the above comment is quite good. Unfortunately enough, it is badly overshadowed by a very simplified personal observation, emotion-driven way of thinking, and above all cynically destructive or unproductive political mentality. I sincerely and strongly want to say that this kind of political mentality must be dealt with a real sense of patriotism ! If anybody is really genuinely and sincerely concerned about any wrong political behavior in the this very patriotic movement of Fanno and all other forces who are making a very remarkable efforts to make not only allied but also United way of doing things , he she must bring it forward in a very smart and productive manner! That is really what the above comment is terribly missing ! Let’s try hard not to repeat and stick with the very ugly and destructive way of doing politics that we have gone through for a very long period of time!!!

    • 100% true, dear T. Goshu. This emotion-led opinion, as you perfectly put it, is the result of our ugly journey for the last 40 or 50 years. And we need time to treat our wounds. But believe me, there is smoke where there is no fire. My fault is the timing. I know timing matters a lot. Thanks for the superb comment you’ve given here. I only regret for the untimeliness of my piece, not of course for the untruthfulness of it. Time will tell us everything.

  3. አቃጣሪ !
    እግዚአብሔር ምንን ይጠላል? “በወንድማማቾች መሐል ጥልን የሚዘራን ሰው” ነፍሱ አብዝታ ትጸየፋለች።

  4. ተረባረባችሁበት ማሳሰቢያ እኮ ነው የሰጠው ፡፡እስክንድር ብዙም ያልተዘመረለት የመላው ኢትዮጵያውያን ምርጫ የሆነ፤ ምንም ሳይጎድለው ለኢትዮጵያ ሲል እድሜ ልኩን የተንከራተተ ምርጥ ዜጋ ነው ስለዚህ የሚገባውን ክብር ይሰጠው ማለት ስህተቱ ምንድነው? እስክንድር እኮ የአዲስ አበባ ልጅ ነው ምቾቱን ጥሎ ነው ምቹ አልጋ ጥሎ ነው ድንጋይና ጫካ ውስጥ የሚያድረው፡፡ ጎበዝ መሪ ካላወጣን ስንከላወስ ነው የምንኖረው ዘመነ ካሴ ቀደም ብሎ የሰጠውን ማብራሪያም ዳግም ማጤን ጥሩ ነው እኔ እያለ ነበር መግለጫ የሚሰጠው፡፡ ቀደም ስላለው ህይወቱም ምስጢር አይደለም ለዛሬ ላይ ስለማይጠቅም ይቅር፡፡ ቢያስችለው ጥሩ የቲም አባል ይሁን ቲሙ ሌሎቹን ለመሪነት እንዳበቃ ሁሉ እሱንም ያበቃዋል እሱም እራሱን ባይሾም መልካም ነው፡፡ ይህንን ስል እሱም አስተማሪ ሁኖ ወይም በንድዶ በቪ8 ሊሄድ እንደሚችልም አውቃለሁ ነገርን የምንመዝነው እንደ ዘመኑ ነውና እስክንድር ይከበር ባለው ጸሃፊ እስማማለሁ፡፡

  5. ትግሉ የህዝብ እንጂ የግለሰቦች የስልጣን ሽኩቻና ግብግብ ወይም የትግል ባለቤትነት የሚረጋገጥበት ጉዳይ አይደለም::ግለሰብ የህዝቡን ትግል ሊቀላቀል ይችላል ይህ ማለት ግን የትግሉ ባለቤት አድራጊና ፈጣሪ ነው ማለት አይደለም መሆንም የለበትም::ግለሰቦች በሚያበረክቱት መጠን እውቅና መስጠት ይገባል ይህ ማለት ግን ይመለክባቸው ማለት አይደለም::በፋኖ ትግል ውስጥ የሚሳተፍ ሁሉም እኩል አክብሮትና እውቅና ሊሰጠው ይገባል::ሁሉም የቆመውና የሚታገለው ለአንድ ዓላማ ነው የሚገብረውም አንድ ህይወቱን ነው::የተግባር ድርሻ ወይም የአመራር ሰንሰለት መኖሩ በችሎታና ተሰሚነት ያላቸውን በመመደብ ለአሰራር ይመቻል በማለት እንጂ ግለሰቦችን ከስልጣን ማማ ላይ ለመስቀል አይደለም::ይህማ ከሆነ ከምንታገለው ስርዓት በምን ይለያል?
    ግለሰቦች በትግል ሜዳ ሊሰዉ ይችላሉ::ትግል ግን አብሯቸው አይሞትም::ይህ የሚሆነው ደግሞ ትግሉ ከግለሰቦች ጋር ያልተሳሰረ ከሆነ ነው::
    አሁን የግለሰቦችን ስብእና ትልቅነት ወይም ትንሽነት እያነሳን የምንጨቃጨቅበት ሁኔታ ላይ አይደለንም::
    ከድል በኽላ የስልጣኑ ባለቤት የሚሆነው የህዝቡን ይውንታ ያገኘ የፓለቲካ መርሃግብር ያለው በምርጫ ያሸነፈ ድርጅት እንጂ የታጠቀ ግለሰብም ሆነ ቡድን አይደለም::ስለሆነም በትግል ወቅት የግለሰቦች አመራር እስከ ድል ድረስ ይሆናል::ከድል በኽላ ትጥቅ ፈተው እንደማንኛውም ዜጋ ከፈለጉ የፖለቲካ ድርጅት አባል ይሆናሉ ድርጅቱም በሚመድባቸው ቦታ ላይ ያገለግላሉ::ከዚያ በተረፈ ትግሉ የግለሰቦች ወይም የቡድኖች አምልኮ የሚንፅባረቅበትና ለስልጣን የሚሻኮቱበት ሊሆን አይገባም::በትግል ውስጥ እያሉ
    ስህተቶች ሊከሰቱ ይችላሉ የተከሰቱ ስህተቶችን በጊዜው ማረም ተገቢ ነው::ስለሆነም በዚህም በዚያም የግለሰቦችን ሚና ከሚገባው በላይ እያጎሉ ወይም እያኮሰሱ መነታረክ ትግሉን ይጎዳል እንጂ አይጠቅምም::በጎጥና በቡድን ጎራ ለይቶ የመከፋፈል አደጋ እንዳይከሰት ሁሉም በንቃት መጠበቅ ይኖርበታል:: ጠላት ሊገባበት የሚችልበት ቀዳዳ መኖር የለበትም::ከግለሰብና ከቡድን በላይ ህዝብምና አገር ሊቀድም ይገባል::ፋኖ ማለት እስክንድር ወይም ዘመነ ወይም መሳፍንት …ወዘተ ማለት አይደለም::ፋኖ ማለት የኢትዮዽያ ዋልታና ማገር የሆነ ህዝባዊ ሰራዊት ማለት ነው::ግለሰቦች በፋኖ ትግል ውስጥ ይገባሉ እንጂ የፋኖ ትግል በግለሰቦች ፈቃድና ፍላጎት ውስጥ የሚገባ የግል ሃብት አይደለም::
    በመጨረሻ ላይ ለማሳሰብ የምወደው እኛ ኢትዮዽያውያን ሃሳባችንን ልንገልፅበት የሚያስችለን በስነፅሁፍ የዳበረ የራሱ ፊደላት ያሉት የአማርኛ ቋንቋ ባለቤቶች ሆነን ሳለ እንደ እንግሊዝ ቅኝ ግዛት አገሮች በእንግሊዝኛ መፃፃፉ በራስ የመተማመንን ስሜት የሚያላላና የጠላቶቻችን አንዱ መንገድ ስለሆነ መታረም እንዳለበት ለመግለፅ እወዳለሁ ::በባእዳን ቋንቋ መጠቀሙ ከውጭ አገር ዜጋ ጋር ለሚኖረው ግንኙነት እንጂ ለእርስ በርሳችን ግንኙነት መሆን የለበትም::የአማርኛና የአማራ ብሎም የኢትዮዽያ ጠላቶች የሚያስተሳስረንን ገመድ ለመበጣጠስ ሲነሱ የሚያነጣጥሩት አንዱ በአማርኛ ቋንቋችን ላይ መሆኑ መዘንጋት የለበትም::ስለሆነም የማንነታችን አንዱ መገለጫችን የአማርኛ ቋንቋችን ነውና አክብረን እናስከብረው::

  6. ውድ የድረገፁ ሙያተኞች በቅድሚያ ሰላምታዬን አቀርባለሁ ቀደም ሲል በዚህ ፅሁፍ ላይ የሰጠሁትን አስተያዬት ልኬ ነበር:: ከእይታ በኽላም እንደሚለጠፍ ጠብቄ ነበር ሆኖም ግን አልሆነም:: ለምን አልተቀበላችሁትም?የጎደለው የአቀራረብና የስነስርዓት ምክንያት ኖሮት ነውን?ምክንያቱ ቢገለፅልኝ ለመታረም ይረዳኛል አስተማማኝና በቂ ምክንያት ከሌለም ቢለጠፍ መልካምና የሃሳብን ነፃነትና የድረገፁን አቃፊነት ያረጋግጣል::
    አመሰግናለሁ
    አገሬ አዲስ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share