September 27, 2023
7 mins read

እንኳን ለመሰቀል በዓል እና መዉሊድም በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን‼️

ዛሬ መስቀልም ነው፣ መዉሊድም ነው።

እንኳን አደረሳችሁ!

378375630 845298806946311 3211979254583976344 n

ለተለያችሁን ጀግኖችም ሆናችሁ ሌሎች ዘመዶቻችን፣ ነፍስ ይማር።

ሳይነኳችሁ ለነካችሁ፣ ሳያባርሯችሁ ለምታሳድዱን፣

በትግስት ሲተዋችሁ በትእቢት ለተሳደባችሁ፣

አላህ ይፍረዳችሁ! ወዳጃችሁ ጋኔል ያባርራችሁ!

የሰላም ጉዞን ለአሰባችሁ እግዜር ይርዳችሁ።

“ጦርነትም ያልፋል። ስለዚህ የመልሶ መቋቋም የሰላም ጉዞ መጀመር ያለበት አሁን ነው።”

በፈለገው ምክንያታዊነት፣ በማንኛውም መመዘኛ ጦርነት ለሰው ልጅ ስቃይ፣ ህይወት መጥፋት እና ውድመት ያደርሳል እንጅ ዘላቂ፣ ስር ነቀል መፍትሔ አያመጣም። ምንም እንኳን አረመኔዎች ባለን ጉልበተኛነት በጦር ኃይል፣ በመግደል ከፍ እንላለን ብለው ሒሳባቸውን ቢያሰሉም፣ ድንቁርናቸው የሚያስከትለውን መዘዝ፣ የረጅም ጊዜ መከራ ከሰው ልጅ  የመተንበይ ግምት ውጭ መሆናቸውን አይተናል። የዘመናት የግጭት ሰንሰለት እንደሚወልድም አይተናል።

ስለዚህ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ በድርድር፣ በዲፕሎማሲ፣ በውይይት፣ በሽምግልና መፈታት አለባቸው።

ቢሆንም፣ የፓሲፊስት ሰማዕታት አመለካከት እንዳለ ሆኖ፣ በጉልበት ብቻ የምፈቱ ግጭቶች በጣም ጥቂት ቢሆኑም አሉ። ብዙውን ጊዜ ጽንፈኛነትንና የተለዩ ሁኔታዎችን ያመለክታሉ። ይህ የመጨረሻ የጦርነት ግዴታ በከፍተኛ ጥንቃቄ እና በአለም አቀፍ ህግ መሰረት መተግበር አለበት። አሳዛኙ ጉዳይ ግን በሰላም መፍታት ያልተቻለው ግጭት መነሻውና ተንኳሹ ሥልጣኔና ሰብዓዊነት የጎደለው ባለግዜ ወይም ደንቆሮ ፅንፈኛ ስለሚሆን ጦርነቱም አስከፊና ሕግም ሆነ ሰባዊነት የጎደለው ይሆናል። ሰላማዊ ሰው መግደል፣ ባጠቃላይ በሴቶችና በሕጻናት ላይ የሚደረገው እንስሳነት፣  አዝርዕትና እንሥሣትን ማቃጠል፣ የገደሉትን መስቀል፣ መቆራረጥ፣ የአረመኔው ጠባይ ነው። ይህንን እያዩ አሸንፈን ቀን ይወጣልናል የሚሉ መሪዎችም ሆኑ ጀሌዎች የአዕምሮ ዝገት ወይ ሻጋታ አለባቸው።

ለሁሉም ጊዜ አለው። ሁኔታዎች ሲንከባለሉ መጥተው፣ የሽምግልና ጊዜ ከሽፎ፣ በትዕግሥት “ከኔ ይቅር፣ ይሁንልህም” ታልፎ፣  አይቀሬው የጦርነት እልቂት ከተጀመረ በኋላ፣ የታመቀ ቁጭት፣ ትኩስ የበደል ቁስል፣ የምያቅለሸልሽ ትዕቢት፣ የሚዘገንን አረመኔንት እየታዬ፣ የእርቅና የሰላም ጥሪ ቦታ አይኖረዉም። በሳጥናኤልና በጊዮርጊስ መካከል እርቅ አይኖርም። ሳጥናኤል ወደገሃነም ካልተላከ በደልና ጦርነት ዘለዓለማዊ ይሆናሉ። የህዋህትን ጉዳይ አየነው አይደለም?

ተጨማሪ ያንብቡ:  2ቱ ብልጽግናዎች ለዳግም የእርስ በእርስ ጦርነት እያሟሟቁ ነው! | Oromia | Dr. Yilkal Kefale | Amhara Prosperity Party

ይህም ሆኖ በርግጥ ጦርነት አንድ ቀን ማቆሙ አይቀርም። የዚያን ጊዜ ለምያስፈልገው ሰላም፣ ለምያስፈለገው ወደ ሰብዓዊነት የመልስ ጉዞ፣ ጉልበትን፣ ንብረትን ማሰባሰብ፣ ያ የሰላም ጥሩ ተልኮ ይሆናል። መጀመር ያለበትም ዛሬ ነው፣ አሁን ነው! የጦርነት ዕብደት አልቆ፣ ሳያዉቅም በድንቁርና፣ እያወቀም ለሆዱ ሲል የበደለ፣ የገደለ ሁሉ መስከን ሲጀምር አንዳንዱ ጥፋቱ ይገባው ይሆናል፤ ይጸጸትም ይሆናል፤ ከጀሌው ውስጥ ማሩኝ የምልም አይጠፋም። ኢትዮጵያዉያን ያንን የሚያስተናግድ ቄስም፣ ዳኛም፣ ሐኪምም፣ ቴራፔውትም፣ መሃንድስም ያስፈለገናል። አሻፈረኝ፣ አላጠፋሁም የሚለውም በወንጀሉ ሲፈረድበት፣ ሰው ነውና ቅጣቱ በአሸናፊው ሌላ ኢሰብአዊ በደል እንዳይፈጠርበት ያኔ ገለልተኛ የሰላም ልኡካን ያስፈልጉናል። በድህነት የማቀቀች አገር የኋሊት ስትሄድ ቢያንስ ወደ ዜሮ የሚያመጣት ኃይል ያስፈልጋታል። ያ ጉልበት ደግሞ በጦርነት ማቆም ማግስት ከሰማይ አይወርድም፤ ከዛሬው መታነጽ፣ መሰልጠን፣ መሰብሰብ፣ መዘጋጀት አለበት። ጊዜ ይቃጠላል፣  ማለትም የድህነት ሞት የባሰ ይከፋል።

ጦርነትም ያልፋል። ስለዚህ የመልሶ መቋቋም የሰላም ጉዞ መጀመር ያለበት አሁን ነው። ለሰላም የተነሳችሁ ወገኖች ጉልበታችሁ በከንቱ እንዳይባክን ወደዝያ ብታዞሩት?

አላህ/እግዚአብሔር  ይችን ያህል አርቀን ማሰብ እንድንችል ሩህ ለግሶን ይሆን?

 

መልካም መውሊድ! መልካም መስቀል!

Yeshiwork Wondmeneh 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

Go toTop