July 21, 2023
2 mins read

ከሰዶም የከፋ እንዲህ ዓይነት ዘመን!

456666 1 1ከጥፋት ውሀና ከገሞራም ከፍተን፣
ጵጵስና ቅብጠት ቅንጦት ሲሆን አየን፡፡

ምንኩስና እርዛት እራብ ነው ቢባሉ፣
እንደ ፈረንጅ ቀበጥ ኬክ ሲገምጡ ዋሉ፡፡

ብፁእ ቅዱስ ነን ብለው የጰጰሱ፣
ተገደን አጳጰስን እየወሸከቱ፤
ተእግዜር እጅ አምልጠው ሰይጣን ጉያ ገቡ፡፡

የሰማዩን ንጉሥ ታዘዙ ቢባሉ፣
ለምድር ገዥ ሎሌ ሆነው ይኖራሉ፡፡

በጋችሁን ጠብቁ ታደጉ ቢላቸው፣
ድሎት ይበላሉ ቀበሮ አሳርደው፡

ሰማእትነት ቢያሳይ ፍሪዳ አድርጎ እራሱን
እነሱ አሳረዱ በግ አርገው ምዕመን፡፡

ፍሪዳው አርጎ ቁጭ ሲል ተእግዜር ቀኝ፣
በግ አሳራጆቹ ሄሮድስ ማረን ማረን፡፡

ከተራራ አውጥቶ ጌታን የፈተነው፣
በአውላላው ሜዳ ላይ አንበረከካቸው፡፡

የክርስቶስን ደም መስቀል አንጠልጥለው፣
ለሄሮድስ ሲሰግዱ አይሰገጥጣቸው፡፡

መጣፈ መነኮሳት መንኑ ቢላቸው፣
ይተም ይፈሳሉ ከተማ ውስጥ ቀልጠው፡፡

አትዩ፣ አታሽቱ አትስሙ ቢባሉ፣
ቀንበጥን ሲመርጡ ሲያሸቱ ያድራሉ፡፡

ተገንዘብ እራቁ ብሎ ቢያዝዛቸው፣
ደሞዝና ዝርፊያ ሆኗል ዝማሬአቸው፡፡

ለቀኖኗ ዶግማ ምዕመናን ታርደው፣
ሲኖሩ አይከብዳቸው እርምን ቅርጥፍ አርገው፡፡

ከሰዶም የከፋ እንዲህ ዓይነት ዘመን፣
ጳጳስ የዓለም ወዳጅ ሰማእታት ምዕመን፡፡

በላይነህ አባተ ([email protected])
ሐምሌ ሁለት ሺ አስራ አምስት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop