የኢትዮጵያ ስትራተጂክ ግርዶሽ: አሜሪካ የበላይነቷን ለማመቻቸት አፍሪካዊ አገልጋይ ገዝታለች – ክፍል 1 ከ 8

aklog birara 1

አክሎግ ቢራራ (/)

አንድ ኒካራጓ እንደሚለው እሱ የውሻ ልጅ ነው፣ እሱ ግን የእኛ ነው።ፕሬዝዳንት ፍራንክሊን . ሩዝቬልት የኒካራጓን አምባገነን ሶሞዛን ሲገልጹ።  በመጀመሪያ በኦነጋዊያን የበላይነት  የሚመራውና የሚታዘዘው መከላከያ ኃይል በቆቦና አላማጣ፤ አማራ ክልል ንጹህ ወገኖቻችን ላይ የፈጸመውን ታሪክ የማይረሳው እልቂት አወግዛለሁ።  ለሰብአዊ ፍጥረት ደህንነት የምትቆረቆሩ ሁሉ ይህንን የጭካኔ ጭፍጨፋ እንድታወግዙ ጥሪ አደርጋለሁ። ይህ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚካሄድ ተከታታይ ግፍና በደል እንዲቆም ከፈተኛ ጥረት እናድርግ እላለሁ።

ኢትዮጵያ ከውስጥዋ እና ከስፌቷ እየፈረሰች ነው። ኢትዮጵያን እንደ ሃገር፤ ኢትዮጵያዊነትን እንደ ዜግነት መለያ የሚደግፍ፣ ሁሉን ያሳተፈና አገር ወዳድ ማዕከላዊ መንግሥት የላትም። የጎሳ ፌደራሊዝም የኢትዮጵያን ብሄራዊ ነፃነት፣ ሉዓላዊነት እና የኢትዮጵያን ህብረተሰብ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያስተሳስረውን የጋራ መድብለ-ሀገራዊ ትስስሮች ሊጠገንና ሊያጎለምስ አልቻለም ። ይህንን ጸረኢትዮጵያ፤ ጸረ-ሰላም፤ ጸረ-ፍትህ፤ ጸረ-አብሮነት፤ ጸረ-እኩልነት፤ ጸረ-ዲሞክራሲ ውርደት የሚፈጽሙት የጎሳ ፖለቲካ እና ማሕበራዊ ልሂቃን – በዋናነት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ኦሮሞ (ኦነግ) ናቸው።  ኃያላን መንግሥታት፤ በተለይ አሜሪካ ከጀርባ ሆነው ከፍተኛ ድጋፍ ይለግሷቸዋል፤  ያዟቸዋል፤ ያሽከረክሯቸዋል። ይህ አስፈሪ እና ሆን ተብሎ የከፋፍለህ ግዛ ሁኔታ ከ1991 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ ነው። ጥልቅና በቀላሉ የማያቆም ነው።

 

የመሪ መለያ ባህሪ፤ ብቃትና ተግባር እንጅ ብሄር አይደለም።  

ቤት እየተናደ እያየ ደንታ-ቢስ የሆነው ሽመልስ አብዲስ የአገዛዝ ግድፈቶችን ምክንያታዊ በሆነ ደረጃ ለሚተቹት ግለሰቦችና ስብስቦች እንዲህ ብሏል። “ዐብይን በኦሮሞነቱ ምክንያት የተነሱበትን የጥፋት እጆች እንቆርጣለን።” ጠቅላይ ሚንስትሩም በአንድ ወቅት እንዲህ ብሎ ነበር። በአዲስ አበብ ከተማ “ኦሮሞ ጠልነት አለ”። እየተናበቡ መስራት፤ እየተናበቡ ማጥፋት ማለት ይኼው ነው።

ለኢትዮጵያ፤ ለኢትዮጵያዊነት፤ ለስብአዊ መብት፤ ለፍትህ፤ ለእኩልነት ለዘላቂና ፍትሃዊ ልማት ወዘተ የቆሙ ኢትዮጵያዊያን ዐብይን በኦሮሞነቱ የተቹበት ወይንም የተቃወሙብት ወቅት ላገኝ አልቻልኩም። ፖሊሲውን፤ ፕሮግራሙን፤ ድርጊቱን፤ እንደ እሥስት ተለዋዋጭነቱን፤ ለሰብአዊ ፍጥረት ደንታ ቢስነቱን፤ ሁሉንም ተግዳሮት በእልቂት፤ በማፈናቀል፤ በጦርነት እንወጣዋለን ወዘተ ባይነቱን ግን የሚቃወመው ክፍል እየተስፋፋ ሂዷል።

ሽመልስ አብዲሳ እንዲመልሰው የምፈልገው ጥያቄ አንድ ነው። ይኼውም፤ በጉጅና በገዲዖ የተነሳው የኦሮሞ ሕዝባዊ እምቢተኛነት የዐብይን ኦሮሞነት በመጥላት ነው? ይህ ከሆነ ሽመልስ አብዲሳ የስንት ሚሊየን ኢትዮጵያዊያንን “እጆች” ሊቆርጥ ነው? አልካይዳ፤ አይሲስ፤ አልሸባብ፤ ቦኮ ሃራም፤ ኦነገ ሸኔ ከሚያደርጉት በምን ይለያል? “እጆች እንቆርጣለን” ብሎ መፎከር ቀይ መስመር ያለፈ እብሪተኛነት፤ ጽንፈኛነት፤ ደንቆረነትና ህሊናቢስነት ነው።

የሽመልስ አብዲሳ ዛቻና ቅስቀሳ የሚያስከትለው አሉታዊ ውጤት አኪል ዳማ ወይንም በአገር ደረጃ ደም መፋሰስን ነው።

 አጀንዳ እየፈበረከ የሚያሳስት አገዛዝ  

ባለፉት ሁለት ሳምንታት የሆነውን ሌላ ጦርነት ቀስቃሽና አመቻች ሁኔታ ላቅርብ። የብልጽግና መንግሥት በፕሪቶሪያና በናይሮቢ  ከህወሃት ጋር የሰላምና ህወሃትን ትጥቅ እንዲፈታ   የተስማማው ውል ከሽፏል ለማለት የሚያስችሉ ሃቆች ሲነገሩ ቆይተዋል። ህወሓት ትጥቅ አልፈታም። የኢትዮጵያ መከላከያ ብሄራዊ ግዴታውን የረሳ በሆነ ደረጃ ትግራይን ለቋል። ህወሃት ትጥቅ እንዳይፈታ፤ ለአራተኛ ዙር ጦርነት እንዲዘጋጅ የተመቻቸው ከጀርባው ምን ሴራ ስላለ ነው? ማንን ለማጥቃት?

ህወሃት ትጥቅ ሳይፈታ የኢትዮጵያ የብልጽግና መንግሥት ለምን ፋኖን፤ የአማራውን ልዩ ኃይል ትጥቅህን ፍታ ብሎ በአማራው ላይ ጦርነት ያካሂዳል ብሎ መጠየቅ አግባብ አለው። የትግራይን መከላከያ ኃይል የመራው ጀኔራል ጻድቃን ምን ሊየደርግና ሊያያመቻች ነው ወደ አሜሪአክ የመጣው? አሜሪካ ለምን የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂ አይሆንም አለች? ለምን የአማራ ፋኖን፤ የአማራ ልዩ ኃይልንና ኤርትራን ለእልቂቶች ሃላፊ አደረገች? ከጀርባው ምን ሴራ አለ?

ባለፉት ሁለት ሳምታት ብቻ በተከታታይ ቁሳቁስ የጫኑ አውሮፕላኖች ከምሽቱ ሶስት ሰዓትና ከጥዋቱ አስራ አንድ ሰዓት ከሱዳን ወደ ሽሬና መቀሌ መብረራቸውን የውስጥ ሁነኛ የመረጃ ሰዎች አረጋግጠዋል። ከዚህ ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል ለህወሃት ድጋፍ እየሰጠ ህወሃት ከባድ መሳሪያና ከፍተኛ የጦር ኃይል ወደ ወልቃይት፤ ጠገዴና ጠለምት ማስጠጋቱ ይነገራል።

ህወሃት እንዲያንሰራራ፤ በራሱ እብሪተኛነትና የሃሰት ትርክት “ምእራብ ትግራይ” ብሎ የፈበረከውን (Fabricated distortions)  የአማራ መሬት መልሶ ለማጠቃለል መሳሪያና ሎጅስቲካ፤ መረጃና ሌላ ለህወሃት የሚሰጡት የውጭና የውስጥ አጋሮች አሉ ማለት ነው። በውስጥ የአቢይ መንግሥት፤ በውጭ ሃያል ወይንም ኃያላን መንግሥታት ይረባረቡበታል። ዶር ደብረጺኦን፤ አለምሰገድ ገብረ-ዋድ፤ ሞንጀሪኖ፤ ጀኔራል ጻድቃን፤ ጌታቸው ረዳ ወዘተ የተስማሙት “ግዳጃችን የተነጠቅነውን መሬት መልሰን ማጠቃለል አለብን” የሚል ነው። የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምትና ራያን መሬት በኃይል ከነዋሪው የአማራ ሕዝብ ነጥቆና የአማራውን ማንነት አውድሞ በብዙ መስዋእት የተመለሰውን የአማራ ማንነት መለያ መሬት መልሸ እወስደዋለሁ ብሎ መዛትና ማስፈራራት እብድነት አይሆንም? ህወሃትና ከጀርባ ሆኖ የሚደግፈው የኦነጋዊያን ፌደራል መንግሥት ከስህተታቸው ለምን አይማሩም?

ተጨማሪ ያንብቡ:  እውን የአማራ ሕዝብ ባርነት የሚወድ ሕዝብ ነው? - መስፍን አረጋ

የአሜሪካ ስትራተጂክ መርህ እንዳለ ሆኖ፤ ዋናውና መሰረታዊው ጥያቄ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል ለምን የሴራው አካልና ደጀን ሆነ? የሚለው ነው። ምክንያቱም፤ መከላከያ ሚናውን ካልሳተ ሃላፊነቱ የኢትዮጵያን ዘላቂና ብሄራዊ ጥቅም መታደግ ነው። ህውሃትና ከጀርባ ሆኖ የሚደግፈው የአሜሪካ መንግሥስት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅምና ለመላው ሕዝቧ ደህንነት እንዳልቆሙ በተደጋጋሚ አይተናል።

ሃሰት ተደጋግሞ ሲነገር እውነት የሆነባት ኢትዮጵያ  

  • ኢትዮጵያ ሃሰት እንደ ተራ ነገር ከሚነገርባቸው የተበከሉ አገሮች መካከል ከፍተኛ ደረጃ ይዛለች። ህወሃት ጭፍን በሆነ ደረጃ አንድ “ሚሊየን የሚሆን የትግራይ ሕዝብ ከወልቃይት ተፈናቅሏል” ብሏል። የሕዝቡ ጠቅላላ ቁጥር ከግማሽ ሚሊየን በታች ከሆነ ይህ ቁጥር ከየት መጣ? ተፈበረከ ማለት ነው። መረን የለቀቀ ውሸት።

 

  • ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ “የህወሃት ጁንታ እንደ ዱቄት በነነ” ብሎ ነበር። እንዴት ሊያንሰራራ ቻለ?

 

  • አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ሂውማንራይትስ ወች በጋራ ጥቂት የትግራይ ተወላጆችን በቴሌፎን አነጋግረው “በምእራብ ትግራይ የዜጎች እልቂት ተካሂዷል” ብለው ፈረዱ። ለአሜሪካ ጣልቃ ገብነት አመቻቹ። በአማራው ላይ የተካሄደውን እልቂት፤ ማይካድራን ጨምረው አላነሱም።

 

  • አመሪካኖች በኢራክ ሳዳም ሁሴንን ለመግደል ባደረጉት ሴራ “የእልቂት መሳሪያ (Weapons of mass destruction” አግኝተናል ብለው ኢራክን ደበደቧት፤ ሳዳምን ገደሉት። እነዚህ የሃሰት ብሂሎች ዋና ኢላማቸው መረጃዎችን ፈብርኮ ጠላትን ማጥቃት ነው።

 

  • ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የዛሬ ሶስት ወር ፋኖን በጽንፈኛነትና ሽብርተኛነት ካወገዘ በኋላ፤ ከገባበት ገብተን እንደመስሰዋለን ብሎ ፎክሮ ነበር። አሁን ደግሞ በረቀቀ የማዘናጊያና ማደናበሪያ ተንኮል ከፋኖ ጋር አጀንዳ የለንም፤ ፋኖ ወደ ፖሊስ፤ መከላከያ ወይንም ወደ መደበኛ ስራው እንዲገባ እንፈልጋለን አለ። ሃቁ የትኛው ነው? ዶሮን ሲያታልሏት እንዲሉ የብርሃኑ ጁላ ታክቲክ ሌለ ይመስለኛል። ለምሳሌ፤ አማራውን በኤርትራ ላይ ለማስነሳት። ወይንም ፋኖ ተዘናግቶ የጀመረውን እንቅስቃሴ እንዲያቆም። እኔ ፊልድ ማርሻሉን የምጠይቀው ኤታ ማጆር ሹም እንደመህንህ መጠን ለምን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር አታስክበርም?

ኢትዮጵያ  በማንኛውም መስፈርት ቢሆን የሞራል ልእልና የሌለባት አገር ሆናለች። ይህ ውድቀት፤ ለአሜሪካ መንግሥት ፋይዳ የለውም።  አሜሪካ የምትፈልገውና የምትመኘው የራሷን ብሄራዊ ጥቅም የሚደግፍን ኃይል ማጠናከር ነው። ይህ አቋም ያዋጣታል የሚል እምነት የለኝም።

በኢትዮጵያና በመላው የአፍሪካ ቀንድ ሰላምና እርጋታ ከተፈለገ፤ ሌላ አውዳሚ ጦርነት እንዲካሄድ ለምን ይመቻቻል? የሚለውን አስኳል ጥያቄ እናስብ። አንዱ ዋና ኢላማ አማራውን ማንበርከክ ነው፤ ወልቃይትን ለህወሃት መልሶ መስጠት ነው። ይህንን ስኬታማ ለማድረግ ደግሞ በተለያየ ጊዜ የተለያየ መፍትሄ ሲቀርብ ይሰማል። ዛሬ የሚለፈፈው የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምትና ራያን የአማራ ሕዝብ የማንነት ጉዳይ “በሕዝብ ድምጽ” እንፍታው የሚል ነው። ሕዝቡ የእማራ ማንነቴ ይከበር አለ እንጅ እንደ ቡራኬ በማንነቲ ድምጽ ልስጥ አላለም። ይህ ሕዝብ ባለፉት አርባ ዓመታት ለክብሩ፤ ለዜግንቱ፤ መብቱና ለማንነቱ ከፍተኛ መስዋእት ከፍሏል፤ ከስዳሳ ሺህ በላይ በህወሃት ተጨፍጭፏል። በኃይል የተነጠቀውን መሬቱንና ማንነቱን አስመልሷል። ማንነት በማንም የሚለገስ አይደለም። ሰብአዊና ዲሞክራሳዊ መብት ነው። አማራውን “ትግሬ እንጅ አማራ አይደለህም” ብሎ መበየን እብደትና እብሪት አይደለም?

የወልቃይት፤ጠገዴ፤ ጠለምትና ራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ የሁሉም አማራ ጥያቄ ነው። ቁም ነገሩ በመላው ኢትዮጵያ ለህልውናው የሚታገለው የአማራው ሕዝብ ለዚህ አዲስ ጦርነት ምን ዝግጅት አድርጓል? የትኛው የውጭ ኃይል ይደግፈዋል? የውስጥ አንድነቱስ ጠንካራ ነው?

የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምት፤ ራያን ከዚያም የጋምቤላን ወዘተ አገራዊ ተግዳሮቶች ስመራመር ባጭሩ ኢትዮጵያ ከድጡ ወደ ማጡ እያመራች ነው እላለሁ። በወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምትና ራያ የሚካሄደው አዲስ ግፊትና የጦርነት ሴራ የሚያሳየው አስኳል ጉዳይ አለ። ይኼውም፤ የኢትዮጵያ የብልጽግና ፓርቲ፣ መንግሥትና የኢትዮጵያ ሃገረ መንግሥት የሀገሪቱን ውድቀት በማጠናከር ረገድ ትልቅ እና ጎጂ ሚና ይጫወታሉ። የውሸትና የማዘናጊያ ንግግሮች ቢኖሩም ኢትዮጵያ አንድ ሀገር አይደለችም። የብልጽግና ፓርቲ መንግስት ወድቋል። ለሕዝብ ህይወት ደንታ እንደሌለው በተደጋጋሚ አይተናል።

አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ በተለይ አማራው በጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድ ላይ ያለው እምነት ሙሉ በሙሉ በኗል። ሊመለስ ወደማይችልበት ደረጃ ተሸጋግሯል። ሕዝቡ በሚናገሩት ውሸት በመበሳጨት ድምጻቸውን መስማት አይፈልግም። ባለፈው ሳምንት ዐብይ አሕመድ በፓርላማው ያደረጉትን ንግግርና ቃለ ምልልስ ስሰማ ይህች አገር እንዴት እዚህ ላይ ደረሰች? ይህ ሕዝብ እንዴት በተከታታይ ሸክምን ችሎ ይኖራል? ብየ ራሴን ጠየቅሁ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የጌታቸው አሰፋ ስውር እጆችና ብሔራዊ አደጋ | ከክንፉ አሰፋ

መሃል ሰፋሪና አያገባኝም፤ እኔን አይመለከተኝም የሚለው ብሂል አያዋጣም። ለሀገርና ለሕዝብ የሚቆረቆሩ ኢትዮጵያዊያን ባለድርሻ አካላት በድፍረትና በፍጥነት ከጎሣና ከፖለቲካ አልፈው በማሰብ ተወያይተው አዋጭ አማራጮችን ማቅረብ አለባቸው። አለያ ታሪክ ይፈርዳል።

አሁን በአብይ መንግስት የተፈታው አሸባሪ ቡድን ህወሀት የትግራይን ክልል ያስተዳድራል። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የሚቆጣጠረው እና የሚገዛው በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ)  ወታደራዊ ክንፍ ብዙ ጊዜ ኦላአ/ሺኔ ተብሎ በሚጠራው ሌላው የጎሳ ልሂቃን አሸባሪ ቡድን ነው። የኦነግ መስራቾች 50  የምስረታ በዓላቸውን ሲያከብሩ “ ለመላው  ኦሮሚያ”  የሽግግር መንግስት  ለመመስረት  መወሰናቸውን  አስታወቁ።  ምክንያታቸውም  ክልላዊ  መንግሥት ፈርሷል፣ አስተማማኝ ያልሆነ፣ሥርዓት የለሽ  እና  ኢ-ዴሞክራሲያዊ   ነው ይላሉ። በሌላ አነጋገር የኦሮሞ የፖለቲካና የማህበራዊ ሃይሎች ፓርቲን፣ ክልልንና መንግስትን በፌዴራል ደረጃ እና በኦሮሚያ ውስጥ ተቆጣጥረው ቢመሩም “የኦሮሞን ጥያቄ” አሁን ክፍተኛ ጥረት አድርጎ ለመመለስ ነው። ትኩረታቸው ኢትዮጵያን ለመታደግ አለመሆኑን በተደጋጋሚ አስመስክረዋል። ኢትዮጵያና ኦሮሙማ ተጻራሪ ናቸው።

 አማራ የኢትዮጵያ ዋና አካል ነው። ኢትዮጵያ ያለ አማራ እና በተቃራኒው አማራ ያለ ኢትዮጵያ የማይታሰብ ነው። ይህን ስኬታማ ለማድረግ ግን አማራው መጀመሪያ ለህልውናው መታገል አለበት። ይህ እውነታ እንዳለ ሆኖ የአማራ ክልል የጦርነት አውድማ ሆኗል። ኦሮሞ የበላይ ሆኖ ሲመራው የነበረውና አሁንም የሚመራው  የኢትዮጵያ ብሄራዊ መከላከያ ሰራዊት — ከእንግዲህ ኢትዮጵያንና ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን በመታደግ የሚሰራ አገራዊ ተቋም ስላልሆነ በአማራው ላይ የሚካሂደው ግፍና በደል፤ እልቂትና ማዋከብ የጦር ወንጀል ነው፣ ዘር የማጽዳት፣ የመድፈር እና የዘር ማጥፋት ወንጀል በአማራ ላይ እየተፈጸመ ነው።

የኦነግ፣ የኦሮሞ ልዩ ሃይል እና አጋር ድርጅቶች 50,000 ንፁሀን የአማራ ተወላጆችን ጨፍጭፈዋል። በወለጋ ኦሮሚያ ብቻ ከአንድ ሚሊዮን በላይ አማራ እንዲፈናቀል አድርጓል። ከህወሃት ጋር ተመሳጥሮ በሰሜን ሌላ ጦርነት እንዲከፈት ለህወሃት ደጀን በመሆን ላይ ይገኛል። ከሱዳን በሌሊትና ጥዋት ቁሳቁስ የያዙ አውሮፕላኖች ወደ ሽሬና መቀሌ ሲበሩ የኢትዮጵያ መንግሥት፤ በተለይ መከላከያ ዳር ድንበሩን ሊጠብቅ አለመፍቀዱ ሴራ እንዳለበት ያሳያል።  ክፍተቱን ላጠናክረው። በየእርስ በእርስ ጦርነት በመሰቃየት ላይ የምትገኘው ሱዳን፤ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ጥሳ የነጠቀቻቸውን መሬቶች እንደያዘች ትገኛለች። በጋምቤላ ከቤት ወጥቶ መግባት ብርቅ ሆኗል። የደቡብ ሱዳን አመጻዊያን የኢትዮፕያን ሉአላዊነት ደፍረው፤ ዳር ድንበር ጥሰው የወረሯቸውን መሬቶቾ ወደ ደቡብ ሱዳን እናጠቃልላን ይላሉ። ይህ ሁሉ ወረራ እየተካሄደ ባለበት ሁኔታ የኢትዮጵያ መከላከያ ምን እየሰራ ነው? ብለን የመጠየቅ ግዴታ አለብን። የኦሮሙማ አጀንዳ ኢትዮጵያን እያፈረሳት ነው የምለው ለዚህ ጭምር ነው።

የአማራን ፋኖ፤ የአማራን ልዩ ኃይልና ሌላውን ለአማራ ህልውና ድምጽ የሚያሰማውን ሁሉ የሚያዋክበው መከላከያ የጋምቤላን ንጹህ ወገኖቻችን ሊታደጋቸው አልቻለም፤ ወይንም አልፈቀደም። ምን አይነት መከላከያ ነው?

በሰሜን ያለውን አደገኛ ሁከት ስመራመረው፤ ሁለት ዓላማዎች ያሉ ይመስለኛል። አንድ፤ አማራውን ማጥቃትና ወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምትና ራያን መልሶ ለህወሃት ማስረከበ፤ ሁሉት፤ የኤርትራን መንግሥት መጣል። የብልጽግናው መንግሥት ለሁለተኛው ግብ ምክንያት የሚሰጠው ኢትዮጵያ የቀይ ባህር በሯን ማስመለስ አለባት በሚል ሺፋን ነው። የህወሃቱ መለስ ዜናዊ ያስረከበውን የባህር በር ለማስመለስ ማለት ነው።

የውጭ ጠላትን በመከላከል ፋንታ፤ የሀገሪቱን መከላከያ ሙሉ በሙሉ በሚያስብል ደረጃ የሚመራው የኦሮሞ ወታደራዊ ኃይል በሁሉም አማራ ላይ ፊቱን አዙሯል።  ሰበቡ የህግ እና ስርዓት መመለስ ነው (Restoration of law and order)። ኢትዮጵያ ህግ አልባ ሀገር ነች። ትክክለኛው የኦሮሙማ አጀንዳና ኢላማ የሆነው ፋኖ፣ የአማራ ወታደራዊ መኮንኖችና ወታደሮች፣ የአማራ ሚሊሻዎች፣ ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች፣ የሲቪክ መሪዎች እና ሌሎችም ጉዳያቸው በህግ ስር እንዳይታይ፣ ሰብአዊ ጥበቃ እንዳይደረግላቸው፣ ርህራሄ እንዳይደረግላቸው እና በተመረጡት ላይ የሚደርሰው ግፍ እንዳይቆምና የዓለም ሕዝብ እንዳያውቀው እየተደረገ ነው። አማራውን ሙሉ በሙሉ ማንበርከክ ነው። ድምጽ አልባ ማድረግ ነው።

ለዚህ ኢላማ የሆነው የአማራ ክፍል በሰው ልጆች ላይ ወንጀል አልፈጸመም። በትኛውም ኢላማዎች የሆኑት አማራዎች አማራ ያልሆኑትን አላጠቁም። የአማራ ተቆርቋሪ፤ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን አላጎረም፤ አልዘረፈም፤ በነፍስ ወከፍ አንድ ሚሊየን ብር ክፈሉ አላለም። ሁሉም የአማራ ኢላማዎች ግን ተጠቂዎች ናቸው። እያደረጉ ያሉት ብቸኛውና ፍትሃዊው ነገር እራሳቸውን እና ማህበረሰባቸውን ከብዙ ክልላዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ወንጀለኞች፤ ሽብርተኞች፤ መከላከል ነው። አማራ የህልውና ስጋት ተጋርጦበታል።

የብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክፍል በሁኔታው እንደተደናገጠ ጥርጥር የለውም። ጥቂቶች የአማራን ጥቅም ከአስፈሪ ውድመቶች  ለመከላከል የቻሉትን ያህል እየሰሩ ነው። ሆኖም፤ ቁርጠኛ  በመሆን፤  ለህሊናችው በመገዛትና ታሪክ እንዳይወቅሳቸው ለማድረግ የአማራን ግፍና በደል ፍትሃዊ ትግል እንዲቀላቀሉ አሳስባለሁ። በተለይ ፊደል የቆጠረው አማራ።  አማራን ማዳን ኢትዮጵያን ከማዳን ጋር እኩል እንደሆነ ማመን አለብን። ዳር ላይ የቆሙት ራሳቸውንም ለማዳን ከፈለጉ ያላቸው አማራጭ የጥፋቱ አካል መሆን ወይንም የሕዝባዊው  አመጽ አካል መሆን ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን የጦር ሜዳ ውሎ ፤ የፖለቲከኞች ጡዘትና የድል ማግስት ተግዳሮቶችና ፈተናዎች 

ሕዝብን መታደግ የተቀደሰ አማራጭ ነው። በማንኛውም አገር ታሪክ የሚሰራው ሕዝብ ነው። የሕዝብን ትግል መደገፍ፤ ቢቻል መቀላቀል ያዋጣል።  የብሪታኒያ የምርመራ ዘጋቢ እና የሰብአዊ መብት ተሟጋች ግሬሃም ፒብልስ “ኢትዮጵያ– ፍርሃትን እየፈጠረች ያለች ሀገር” Counterpunch፣ July 3, 2023 በተሰኘው እጅግ የሚያስመሰግነው እና ወቅታዊ  ትችቱ ላይ እንደፃፈው የተሻለ፣ ፍትሃዊ፣ አገዛዝን መሰረት ያደረገ፣ ሁሉን አቀፍ እና ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን የመምራት ደስታ እና ተስፋ በጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ቁጥጥር ስር ያለችው ኢትዮጵያ ወደ ቀጭን አየር ተንናለች። “– የአብይ እና የአገዛዙ እውነተኛ አፋኝ ቀለሞች ተገለጡ፤ ከአመት አመት እየተጠናከረ የመጣ የቁጥጥርና ከፋፋይ ዘዴ”  ነው ብሎታል።

ለዚህ አገራዊ ጥፋት፤ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ እንደተናገረው “ተበላን፤ ሁላችንም አጥፍተናል፤ ከጥፋታችን እንማር፤ በቃን” ወዘተ ትክክል ነው።  የአሁኑ አገሪቱን በጭፍን፤ በእብሪት፤ በጉራና በድንቁርና የሚመራው ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባል።

ኃይለ ማሪያም ደሳለኝ ቀደም ሲል የዐብይ ሥልጣን መያዝ “የፈጣሪ ተልእኮ ነው (Divine Intervention)” ያለውን ቢስብ ጥሩ ነበር። ይህ እንዳለ ሆኖ ግን፤ የአሁኑ ጠቅላይ ሚንስትር በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለም ደረጃም ተንቋል። ራሱ ተንቆ አገራችንም እንድትናቅ አድርጓታል። በአማራው ሕዝብ ለይ የሚካሄደው አረመኒያዊ ግፍና በደል ብቻ ሳይሆን፤ የኢትዮጵያ ዳር ድንበር፤ የኢትዮጵያ ሉዐላዊነት ተደፍረዋል።  ለዚህ ሁላችንም ተጠያቂዎች ነን::

ታላቁ የድብቅ ሴራ

አሜሪካኖች የሚመኙት ዐቢይንና ህውሃትን አገልጋይ አድርገው በአማራውና በኤርትራ መንግሥት ላይ ጥቃት ማካሄድ ነው። ይህ ተከታታይ ትውልድና ታሪክ የማይረሳው ክህደት ነው። ህወሃት ለአራተኛ ጊዜ ለጦርነት እየተዘጋጀ ነው። ትጥቅ እንዲፈታ ያስገደደው ኃይል የለም። ተገን ሆኖ ትጥቅና ወታደር ወደ ወልቃይት፤ ጠገዴና ጠለምት እንዲያጓጉዝ የሚያመቻችለት በኦሮሞ የበላይነት የሚመራው መከላከያ መሆኑ ተረጋግጧል። የፕሪቶሪያውና የናይሮቢው ስምምነት አሉትዊ ውጤት ይኼ ሆኗል ብል አልሳሳትም።  አማራው ተክዷል። ኢትዮጵያም ተክዳለች። ህወሃትም፤ የብልጽግና ፓርቲም ከዚህ ክስና ወቀሳ ሊወጡ የሚችሉበት ሁኔታ አይታየኝም።

እኔ “ሕዝበ ውሳኔ” የሚለውን ተንኮል የተሞላበት አማራጭ አልቀበልም። ህወሃት ወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠልምትና ራያን በኃይል ሲወስድና ነዋሪውን የአማራ ሕዝብ “አንተ ትግሬ እንጂ አማራ አይደለህም” ብሎ ሲወስን “ሕዝበ ውሳኔ” አካሂዶ ነው? ከስድሳ ሽህ በላይ የሚገመት አማራ ሲጨፈጭፍ፤ ብዙ ሽህዎችን ከቀያቸው ሲያባርር “ሕዝበ ውሳኔ” አድርጎ ነው? ወረራና የዘር ጭፍጨፋ በዓለም መንግሥታት የተወገዘ ነው።

ጌታቸው ረዳ ካለፈው የህወሃት ስህተትና ጥፋት አልተማረም። ሊማርም አይችልም። “ሂሳብ እናወራርዳለን” ምን ማለት ነው? ከዘር ማንዝራችሁ እንጨፈጭፋችኋለን ማለት ነው። ተጨማሪ ግፍና በደል ማለት ነው። ይህንን የሚቀበል አማራ የለም።  ህወሃት ሌላው ቀርቶ “በሕገ መንግሥቱ መሰረት” በወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምትና ራያ ጉዳይ ላይ “ህዝበ ውሳኔ” ይደረግ የሚለውን፤ የአማራው ክልል አመራር የተቀበለውንና ያቀረበውን የተሳሳተ አማራጭም አልቀበልም ብሏል። ይህ ወደ የት እንደሚመራ ግልጽ ነው። ወደ ጦርነት። የዐብይ መንግሥት ወደ ጦርነት ልንሄድ አንችልም፤ አንፈቅድም ይል ይሆን? በቅርቡ እናውቀዋለን።

ከጀርባው ያለው የህወሃትና የኦነጋዊያዊያን ፍላጎት ግን የአሜሪካን ፍላጎት ስኬታማ ለማድረግ ወደ ጦርነት የሚለውን መርህ ቢቀበሉ አልደነቅም። ዋናው ግብ አማራውንና የኤርትራን መንግሥት ማጥቃት እንደሆነ እገምታለሁ።  የተኮላሸ ራእይና ተልእኮ ዐቢይ አህመድ  የኢትዮጵያ ብሩህ፣ ሁሉን አቀፍ እና የብልጽግና የወደፊት መሀንዲስ ነው ብለው ካመኑ ተሳስተዋል።

ሰብአዊነቱ፣ ፍትህ፣ ፍትሃዊ እና እኩልነት፣ የህግ የበላይነት እና የኢትዮጵያን የነጻ እና የተባበረች ሀገር ሆና እንድትቀጥል ቁርጠኛ አቋም በመያዝ ፋንታ፤ አሁን ቀውሱን ያባባሱት በምትኩ (ህወሃት ከፈረሰ በኋላ) የኦሮሞ ብሄርተኝነት አራማጆች መሆናቸውን በመሬት ላይ ያሉ አመልካቾች ሁሉ ያሳያሉ   ዘውጋዊ ተተኪነት፤ የበላይነት፤ ትምክተኛነት፤ አይን ያወጣ እርቢተኛነት እና ተግዳሮቶችን ሁሉ ጭካኔ በተሞላበት ወታደራዊ አሸናፊነት ለመወጣት መሞከር አያዋጣም። ይህ መርህ፤ ሰፊውን የኦሮሞን ሕዝብም አይወክልም፤ አይመጥንም።  

ይቀጥላል

July 13, 2023

 

 

3 Comments

  1. FOR ETHIOPIAN SOVEREIGNTY NOT ONLY THE ISSUE OF AMAHARA PEOPLE ONLY. IT IS THE RESPONSIBILITY OF ALL ETHIOPIAN TRIBE, THEN OTHER TRIBES MUST SUPPORT AMHARA PEOPLE

  2. Aklog birra said

    “ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ “የህወሃት ጁንታ እንደ ዱቄት በነነ” ብሎ ነበር። እንዴት ሊያንሰራራ ቻለ?”

    እርሶም እኮ አቢይ አመድን “ለመጀመርያ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስቴር የምለው መሪ አገኘሁ ብለው” ሙሴነቱን ነግረውን ነበር ዋሽንግተን ዲሲ ስብሰባ ላይ!

    እርሱ አያፍር እርስዎም እፍረት የሚባል ነገር ስላልፈጠረብዎች ይቅርታ እንኳን አልጠየቁም ለካድሬነትዎ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share