የዐማራ ኅልውና ቃል-ኪዳን

July 7, 2023

Amhara

ግንቦት ፪ ሽህ ፲፭ ዓ/ም

“የዐማራ ኅልዉና ቃል-ኪዳን” ባለፉት ሁለት ትውልዶች የዐማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ የገጠሙትን የኅልውና ተግዳሮቶች በሚገባ አስገንዝቦ አብረው የመጡ ዕድሎችን ለመጠቀም፣ አደጋዎችንም ለመቋቋም የሚያስችሉ ስልቶችን የሚጠቁም አቅጣጫ ሰጭ ሰነድ ነው። በዘመን ተሻጋሪ የወል እይታ የዐማራ ሕዝብ ማንነትን፣ ዕጣ- ፈንታውንና ሰቆቃ የወለደውን ንቃተ-ኅሊና በተጨባጭነት ይተርካል። በተለይም የዚህን ትልቅና ታላቅ ሕዝብ ታሪካዊነት፣ አኩሪ ስልጣኔ፣አብነታዊ እሴቶች፣ የፖለቲካ ማንነትና መሠረታዊ ጥቅሞችን ጨምቆ ያቀርባል።

ስለዚህም ዐማራዊ ድርጅቶችም ሆኑ ንቅናቄዎች የሕዝቡን ርቀተ-ሰፊ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥቅሞችን አገናዝበው፤ “ዐማራነት መነሻችን፣ ኢትዮጵያዊነት መዳረሻችን” በሚል ብሒል እንዲታገሉ የሚረዳ የወል ራዕይን ይነድፋል። በተለይም በቅርቡ በፌደራል መንግስት የታዎጀበትን ጦርነት በዘላቂነት ለማሸነፍ ጠንካራ ድርጅትንና መሪዎች ማፍራት፣ ፍሬያማ ስልቶችንና ከመስዋዕትነት በኋላ ለሚገነባው ነጻና የበለጸገ ህብረተሰብ ፍኖተ-ካርታ እንዲነደፍም አቅጣቻዎችና አስቸኳይ ጥሪ ያቀርባል።The Amara Freedom Charter_May 2023

——

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop