June 12, 2023
6 mins read

ፍሬ አልባ ደረቅ ዛፍ ላይ ድንጋይ ማባከን ለምን ?

252 153023 fb img
#image_title

ዕንግዳ ተቀባዮች እንደነበርን መረሳቱስ ፡፡ ዛሬ ላይ ይህ ዕንግዳ ተቀባይነት ታሪክ ቢሆንም በአዴን ላይ መኖሩ የሚደንቅ ባይሆንም የሚጠበቅ ነዉ ፡፡

አሁን ደግሞ የትህነግ ጊዜያዊ አስተዳዳሪ ባ/ር መገኘት እና መነጋገር ለምን እንደ ድንቅ እና ብርቅ መናፈሱ የሚገባ አይደለም የምን መደናነቅ ነዉ ፡፡

በልቶ ዝም የሚል ጌታዉን የሚክድ ሎሌ አይኖርም እና በአዴን መቀሌ የብዙዎች ኢትዮጵያዉያን እና አማራ  ደም እና መቃብር ረግጦ መቀሌ ተገኝቷል፡፡

የሆነዉ ግመል ሰርቆ አጎንብሶ መሄድ የለም እና  ጌታዉን የሚያገለግል ህዝብን የሚገለገል በባርነት የተያዘ ምንዱባን ላይ መፍረድ የደረቀ ዛፍ ፍሬ አልባ ዛፍ ላይ ድንጋይ ማባከን ለበጎ አይደለም፡፡

ይህ ኢትዮጵያን በማዉድም እና አችና በማክሰም  ኢትዮጵያን በማድማት ትግራይን ማልማት ለሰላሳ ዓመታት መሰራቱ እና ይህም በበአዲን ጉዳይ አስፈፃሚነት መሰራቱን እንዴት ተዘንግቶ ነዉ ብሎ መጠየቅ እና ታሪክን ወደ ኋላ ማወቅ እንዴት ይዘነጋል ፡፡

በአዲን በምናብ የሚያስተዳድረዉ የሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ (ሠም-ኢትዮጵያ) ከነሰያሜዉ ሳይቀር ዓማራ ክልል ብሎ የተሰጠዉን እንደወረደ ያለምንም ቀቅድመ ጥያቄ ፈራ ተባ ሳይል ዓማራ እያለ የዓማራን እና የኢትዮጵያን ሙሉ ጥቅም እና ታሪካዊ ዳራ አሳልፎ ለመስጠጥት ቀደምት ተባባሪ መሆኑን ዓለም ሲያዉቀዉ የጎንደርን እና የወሎን ግዛቶች አሳልፎ ለመስጠጥ መጠራጠር  ሰዉ አለመሆን ነዉ ፡፡

ይህ በኢትዮጵያ እና ህዝቦች ኪሳራ በተለይም በዓማራ ህዝብ ነፃነት እና ህልዉና በተከፈለ ዋጋ ለትህነግ /ኢህአዴግ አሳልፎ መስጠት የበአዴን መገለጫ ነዉ ፡፡

ከኢህአዴግ መስረታ (1982) ጀምሮ በኢትዮጵያዉያን ደም እና ህይወት በተከፈለ ሁለንተናዊ መስዋዕት ወርቅ በጨርቅ የመለወጥ ፣ በክልሉ ከወረዳ አስከ ክልል ርዕሰ መስዳደር በቀጥታም ሆነ በሌላ ሁኔታ የሰሜን ምዕራብ ግዛቶች በኢትዮጵያዉያን ዓማራዎች አመራር ስር ሆነዉ ያዉቃሉ ወይ ፡፡ ለመሆኑ ኢህአዴግ ወይም ብአዴን ህልዉናዉን በአስራ ዘተኝ መቶ ሰማንያ ሶስት ካጣ በኋላ በነቢብ እጂ በሀሳብ እና በተግባር አለ ወይ ፡፡

ማነዉ ኢትዮያን ለትህነግ የግል ንብረት አሳልፎ የሰጠ ፣ ማነዉ የኢትዮጵያ ህዝባዊ ብሄራዊ ጦር (ምድር፣ሰማይ ፣ባህር..) እንዲከስም ፣ የዓማራዉ ህዝብ ሶስተኛ ዜጋ እንዲሆን ….ያደረገዉ ብሎ መጠየቅ እና ማወቅ ዛሬ ሳይሆን ከሀያ ዓመት በፊት መታወቅ የመበረበት ነዉ ፡፡

ኢህአዴግ እያለ  ብአዴን ምን የተለየ ሚና ይጠበቅበታል ፡፡ ዕዉነት ብአዴን ለአቅመ  ራስን መቻል የበቃ እና በቦታዉ ቢኖር የቀደመዉን ትተን የዛሬዉን እንይ  ትህነግ አገር ወሮ ፣ አገር ገድሎ ፣ ህዝብ በድሎ …..ከነሙሉ ጥቅሙ እና ስሙ የክልሉን መከለሳከያ (የትግራይ መከላከያ) በአባልነት ያለበት ፣ የወረራዉ ፊዉታራሪ የነበሩት የወታደር አዛዥ ምክትል አስተዳዳሪ በሆኑበት  የሽግግር መንግስት ሲመሰርት ብአዴን በጭንቅ ጊዜ የኢትዮጵያን ፣ የዓማራን እና የኢህአዴን ህልዉና  ከጥፋት እና ከሞት የታደገ የዓማራን ህዝብ ፤ልጆች (ልዩ ኃይል፣ ፋኖ ፣ መከላከያ…..) ወዘተ በማዳከም ህዝቡን እና ልጆችን አመድ አፋሽ ማድረግ ነበረበት ወይ ፡፡ አትፈርዱ ብአዴን በዕዉነት ኖሮም ፤ታይቶ አይታወቅም እና አትፈረዱ “ድንጋይ የሚወረወረዉ ፍሬ በያዘ ዛፍ ነዉ እና” ድናጋይ ማባከን ነዉ፡፡

ብአዴን ህዝባዊ እና ብሄራዊ ጀግኖችን ( ሙሉዓለም አበበ፣ ዶ/ር ዓምባቸዉን፣ ጀ/ል አሳምነዉን፣ አስማረ ዳኘ……) እና የራሱን አጋር ጓዶች ወደ ጎን ትቶ ለአገር እና ለህዝብ ጠንቆች ሙሾ አዉራጂ  ማህበር በአድረ ባይነት እና በበታችነት አስተሳሰብ ለተጠፈነ ገ ድርጂት  ፍሬ አልባ ዛፍ መሆኑን ዘንግቶ ድንጋይ መወርወር ከንቱ የዕንቅልፍ ሩጫ ነዉ ፡፡

“ከፍሬያቸዉ ታዉቋቸዋላችሁ ፡፡”

“የጦር የጦር ለታ አንተን ያሉ ሁሉ ፣

ዓማን ቢሆን ነዉ ወይ ጥለዉህ የበሉ ፡፡”

 

አንድነት ኃይል ነዉ !

Allen T. Silassie !

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop