ፍሬ አልባ ደረቅ ዛፍ ላይ ድንጋይ ማባከን ለምን ?

252 153023 fb img
#image_title

ዕንግዳ ተቀባዮች እንደነበርን መረሳቱስ ፡፡ ዛሬ ላይ ይህ ዕንግዳ ተቀባይነት ታሪክ ቢሆንም በአዴን ላይ መኖሩ የሚደንቅ ባይሆንም የሚጠበቅ ነዉ ፡፡

አሁን ደግሞ የትህነግ ጊዜያዊ አስተዳዳሪ ባ/ር መገኘት እና መነጋገር ለምን እንደ ድንቅ እና ብርቅ መናፈሱ የሚገባ አይደለም የምን መደናነቅ ነዉ ፡፡

በልቶ ዝም የሚል ጌታዉን የሚክድ ሎሌ አይኖርም እና በአዴን መቀሌ የብዙዎች ኢትዮጵያዉያን እና አማራ  ደም እና መቃብር ረግጦ መቀሌ ተገኝቷል፡፡

የሆነዉ ግመል ሰርቆ አጎንብሶ መሄድ የለም እና  ጌታዉን የሚያገለግል ህዝብን የሚገለገል በባርነት የተያዘ ምንዱባን ላይ መፍረድ የደረቀ ዛፍ ፍሬ አልባ ዛፍ ላይ ድንጋይ ማባከን ለበጎ አይደለም፡፡

ይህ ኢትዮጵያን በማዉድም እና አችና በማክሰም  ኢትዮጵያን በማድማት ትግራይን ማልማት ለሰላሳ ዓመታት መሰራቱ እና ይህም በበአዲን ጉዳይ አስፈፃሚነት መሰራቱን እንዴት ተዘንግቶ ነዉ ብሎ መጠየቅ እና ታሪክን ወደ ኋላ ማወቅ እንዴት ይዘነጋል ፡፡

በአዲን በምናብ የሚያስተዳድረዉ የሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ (ሠም-ኢትዮጵያ) ከነሰያሜዉ ሳይቀር ዓማራ ክልል ብሎ የተሰጠዉን እንደወረደ ያለምንም ቀቅድመ ጥያቄ ፈራ ተባ ሳይል ዓማራ እያለ የዓማራን እና የኢትዮጵያን ሙሉ ጥቅም እና ታሪካዊ ዳራ አሳልፎ ለመስጠጥት ቀደምት ተባባሪ መሆኑን ዓለም ሲያዉቀዉ የጎንደርን እና የወሎን ግዛቶች አሳልፎ ለመስጠጥ መጠራጠር  ሰዉ አለመሆን ነዉ ፡፡

ይህ በኢትዮጵያ እና ህዝቦች ኪሳራ በተለይም በዓማራ ህዝብ ነፃነት እና ህልዉና በተከፈለ ዋጋ ለትህነግ /ኢህአዴግ አሳልፎ መስጠት የበአዴን መገለጫ ነዉ ፡፡

ከኢህአዴግ መስረታ (1982) ጀምሮ በኢትዮጵያዉያን ደም እና ህይወት በተከፈለ ሁለንተናዊ መስዋዕት ወርቅ በጨርቅ የመለወጥ ፣ በክልሉ ከወረዳ አስከ ክልል ርዕሰ መስዳደር በቀጥታም ሆነ በሌላ ሁኔታ የሰሜን ምዕራብ ግዛቶች በኢትዮጵያዉያን ዓማራዎች አመራር ስር ሆነዉ ያዉቃሉ ወይ ፡፡ ለመሆኑ ኢህአዴግ ወይም ብአዴን ህልዉናዉን በአስራ ዘተኝ መቶ ሰማንያ ሶስት ካጣ በኋላ በነቢብ እጂ በሀሳብ እና በተግባር አለ ወይ ፡፡

ማነዉ ኢትዮያን ለትህነግ የግል ንብረት አሳልፎ የሰጠ ፣ ማነዉ የኢትዮጵያ ህዝባዊ ብሄራዊ ጦር (ምድር፣ሰማይ ፣ባህር..) እንዲከስም ፣ የዓማራዉ ህዝብ ሶስተኛ ዜጋ እንዲሆን ….ያደረገዉ ብሎ መጠየቅ እና ማወቅ ዛሬ ሳይሆን ከሀያ ዓመት በፊት መታወቅ የመበረበት ነዉ ፡፡

ኢህአዴግ እያለ  ብአዴን ምን የተለየ ሚና ይጠበቅበታል ፡፡ ዕዉነት ብአዴን ለአቅመ  ራስን መቻል የበቃ እና በቦታዉ ቢኖር የቀደመዉን ትተን የዛሬዉን እንይ  ትህነግ አገር ወሮ ፣ አገር ገድሎ ፣ ህዝብ በድሎ …..ከነሙሉ ጥቅሙ እና ስሙ የክልሉን መከለሳከያ (የትግራይ መከላከያ) በአባልነት ያለበት ፣ የወረራዉ ፊዉታራሪ የነበሩት የወታደር አዛዥ ምክትል አስተዳዳሪ በሆኑበት  የሽግግር መንግስት ሲመሰርት ብአዴን በጭንቅ ጊዜ የኢትዮጵያን ፣ የዓማራን እና የኢህአዴን ህልዉና  ከጥፋት እና ከሞት የታደገ የዓማራን ህዝብ ፤ልጆች (ልዩ ኃይል፣ ፋኖ ፣ መከላከያ…..) ወዘተ በማዳከም ህዝቡን እና ልጆችን አመድ አፋሽ ማድረግ ነበረበት ወይ ፡፡ አትፈርዱ ብአዴን በዕዉነት ኖሮም ፤ታይቶ አይታወቅም እና አትፈረዱ “ድንጋይ የሚወረወረዉ ፍሬ በያዘ ዛፍ ነዉ እና” ድናጋይ ማባከን ነዉ፡፡

ብአዴን ህዝባዊ እና ብሄራዊ ጀግኖችን ( ሙሉዓለም አበበ፣ ዶ/ር ዓምባቸዉን፣ ጀ/ል አሳምነዉን፣ አስማረ ዳኘ……) እና የራሱን አጋር ጓዶች ወደ ጎን ትቶ ለአገር እና ለህዝብ ጠንቆች ሙሾ አዉራጂ  ማህበር በአድረ ባይነት እና በበታችነት አስተሳሰብ ለተጠፈነ ገ ድርጂት  ፍሬ አልባ ዛፍ መሆኑን ዘንግቶ ድንጋይ መወርወር ከንቱ የዕንቅልፍ ሩጫ ነዉ ፡፡

“ከፍሬያቸዉ ታዉቋቸዋላችሁ ፡፡”

“የጦር የጦር ለታ አንተን ያሉ ሁሉ ፣

ዓማን ቢሆን ነዉ ወይ ጥለዉህ የበሉ ፡፡”

 

አንድነት ኃይል ነዉ !

Allen T. Silassie !

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop