መምህር ኃይለ ማርያም የታፈኑት እውነት በመናገራቸው ነው – ብርሃኑ አድማስ

ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው።

“ራስህን በእውነት አስጊጥ፣ በሁሉም ጉዳይ እውነትን ብቻ ለመናገር ሞክር፣ የሚጠይቅህ ማንም ይሁን ማን ለሐሰት ድጋፍ እትስጥ። አንተ እውነቱን በመናገርህ የሚናደድብህ ሰው ቢኖር እንዳትዝን፤ ይልቁንም “ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና /ማቴ 5፥ 10/ በሚለው የጌታህ ቃል ራስህን አጽናና ።

/ቅዱስ ገናዲየስ ዘቁስጥንጥንያ /
መምህር ኃይለ ማርያም የታፈሩት ክህነት መነገጃ ለሚያደርጉት አይሰጥ በማለታቸው ነው። መምህር ኃይለ ማርያም የታፈኑት ቤተ ክርስቲያንን ቤተ ክርስቲያን ከሚያሰኙት ዋናው ሥርዓተ ክህነት በቀኖና ቤተ ክርስቲያን ይፈጸም በማለታቸው ነው። መምህር ኃይለ ማርያም የታፈኑት በመምህር አምላክ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ይዘግይ በማለታቸው ነው። መምህር ኃይለ ማርያም ሥራቸውን ከመሥራት ኃላፊነታቸውን ከመወጣት፣ ቃለ እግዚአብሔር ከማስተማር እና ለቤተ ክርስቲያን ጥብቅና ከመቆም ውጭ ወንጀል የሚፈጽሙ ሰው አይደሉም።
ስለዚህ ያሳፈኗቸው አሁኑኑ ጵጵስናን በጫና ማሰጠት የሚፈልጉ፣ እውነት ስትነገር የሚደነብሩ፣ ክህነትን ለፖለቲካ እና ለጥቅም መነገጃ ማድረግ የሚፈልጉ እና ይህም እንዲፈጸም የጥቅም ትስስር ባላቸው አካላት ጥቆማ መሆኑን ለመረዳት አያስቸግርም።
እንኳን በዚህ ዘመን እና በእኛ ሀገር ይቅር እና በየትኛውም ዘመን እና ሁኔታ የተፈጸመ ድብቅ ምክር እና ተንኮል ሁሉ መገለጡ አይቀርም። የማይገለጥ የተከደነ፣ የማይታወቅ የተሠወረ የለም ተብሏልና። ስለዚህ መምህሩን ፍቷቸው። እውነትንም አጥብቃችሁ አታሳድዷት። ሐሰትንና ተንኮልንም አታክብሯት። በኋላ ለፍርድ አሳልፈው ይሰጧችኋልና።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ገዥዎቻችንና የሃይማኖት አባቶቻችን ከየት ነው የመጡት? - ፊልጶስ

1 Comment

  1. ባቢሌ ቶላ በነጮች አቆጣጠር በ 1997 To Kill a Generation በተሰኘው መጽሃፉ ላይ በደርግ ጊዜ የነበረውን ሰቆቃና ወያኔ አለቃ ከሆነ በህዋላም የተገነዘበውን የጊዜው ገዳይና አፋኝ በሌላው እንደተተካ በመዘርዘር ያለፈ መከራንና መጭውን ሁኔታ አመላክቶናል። የሚያስገርመው በመጽሃፉ ላይ ጸሃፊው ያመላከታቸው ነገሮች አሁንም በሃበሻዋ ምድር እየተደገሙ መሆናቸው ነው። ጠልተው እያስጠሉ፤ ለነጻነት በማለት ነፍጥ አንስተው ዞረው ተመልሰው የመከራ ዶፍ በህዝባችን ላይ የሚያዘንቡት እነዚህ የዘመኑ የብሄር ሰካራሞች መድሃኒት በማይገኝለት በሽታ የታመሙ የእድሜ ልክ ድውያን ናቸው። በማፈን፤ በመግደል፤ በመሰወር፤ በማሰቃየት፤ ቤት እያፈረሱ ውጡ በማለትና አልፎ ተርፎም በመግደልና በማሳደድ ምንም አይነት ሃይል በስልጣን ላይ ለዘለቄታ መቆየት አይችልም። ያ ቢሆን ኑሮ ደርግና ወያኔ ዛሬም በየስፍራቸው በተገኙ ነበር። ያኔ ከባህር ማዶ በተሻገረ ርዪተ ዓለም ሲጠዛጠዝና በብሄር ነጻነት ስም ባንክ ሲዘርፍ፤ ህዝብ ሲጨፈጭፍ፤ ድልድይ ሲያፈርስ የነበረው አሁን በየቦታው ተሰክቶ ሥራቸው ሁሉ በዘር፤ በክልል፤ በቋንቋ፤ በሃይማኖት ወዘተ የተለወሰ በመሆኑ ሰው በሰውነቱ መመዘኑ ቀርቷል። ከሰለጠኑ አይቀር እንዲህ ነው። እያደሩ መደንቆር! ለይቶልን እንደ እንስሳት መሆን። በጥቅሉ የብሄር ነጻ አውጭዎች ራሳቸው በጥላቻ ገመድ የታሰሩ፤ አርቆ ማሰብ የማይችሉ በስማቸው ቅጥያ ዶ/ር፤ ፕሮፌሰር፤ ኢንጅኒየር ገለ መሌ የሚል ለጥፈው በደንበር ገተር የሚርመሰመሱ ሙታኖች ናቸው።
    አሁን እንሆ መምህር ኃይለ ማርያምንና ሌሎችን ያፈነው ሃይል ተግባር ዞሮ ተመልሶ ሲሰላ መደመሩ ቀርቶ እየመረጡ መቀነስ እንደሆነ የየቀኑ ወሬ ይነግረናል። የሚያሳዝነው አሁንም የሚነገደው በብሄር ስም መሆኑ ነው። በየጊዜው በመግለጫ ጋጋታ ያደነቆሩን እነዚህ የሰው እንስሳዎች አጠገባቸው ሰው ጦሙን እያደረ እነርሱ ለጊዜውም ቢሆን ጮማ የሚያማርጡበት ሁኔታ ላይ ናቸው። ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ካለፈው የቅርብም ሆነ የሩቅ ታሪክ ትምህርት መውሰድ አለመቻላቸው ነው። ጎረቤት ሃገር ሱዳን እንዲህ ከመታመሷ በፊት ይህ እንደሚመጣ አልፎ አልፎ ሰዎች ተናግረው ነበር። በዳርፉር ብዙ ግፍ የፈጸመው የዛሬው ፈጣን ሃይል (RSF) የትላንቱ (Janjaweed militias) ያኔ የሱዳን መሪ በነበሩት በኦማር አልባሽር ታጥቆ ስልጣን የተሰጠው የገዳዪች ስብስብ ነበር። አሁንም ነው። ይህ ሃይል ነው አሁን ከሚፋለመው ከሱዳን ሰራዊት ጋር አብሮ አልባሽርን ከስልጣን ያወረደው። ይኸው እንሆ አሁን ደግሞ በጋራ ምድራቸውን ወደ አመድነት እየለወጡ ነው። ለዚህ ነው ፓለቲካ የወስላቶች ስብስብ ነው የምለው። ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ። አሁን በሃበሻዋ ምድር የተዘረጋው የአፓርታይድ አገዛዝ እያባላን ያለው እሳት ቡግ ብሎ በመንደድ ሁሉን የሚያዳርስ እንደሚሆን ከአሁኑ መገመት ይቻላል። ማን እየሞተ፤ እየተሰደደ፤ እየታረሰ፤ ንብረቱ እየታገደ እጅና እግሩን አጥፎ ኑና እንደፈለጋችሁ አርጉኝ ብሎ ይቀመጣል? አብሮ መኖር ለማይሹ ጠባብ ብሄርተኞች እሳትን በእሳት መመለሱ አልሞት ባይ ተጋዳይነት እንጂ ጠብ ፈላጊነት አይደለም። ስንት ግፍ የሰራው የኦነግ ሰራዊት ጋር ድርድር እያለ በሰሜኑ ውጊያ አብረው ከሰራዊቱ ጋር የተዋደቁትን የፋኖ፤ የአማራ ሚሊሻ፤ የአማራ ልዪ ሃይል በአሜሪካና በወያኔ ትዕዛዝ አሁን ትጥቅ ፍቱ በማለት መላ የአማራን ህዝብ ማሸበር ሆን ተብሎ የሚሰራ የክፋት እቅድ እንጂ የአማራ ህዝብ ታጠቀም አልታጠቀም ሌላውን አጥቅቶ አያውቅም። ያ ሲልለት እርስ በራሱ ከመገዳደል ውጭ። ግን ይገባናል፤ እንረዳለን በአማራና በኢትዪጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ላይ የታወጀው ጦርነት ኢትዮጵያን ለማጥፋት እንደሆነ። ግን ይህም ያልፋል። ስንት መከራ በምድሪቱ አልፎ የለ። ያው የሚያለቅሰው ያነባል፤ የተራበው ይራባል፤ የሚዘርፈው ይዘርፋል፤ የሚሞተው በየሰበቡ ይሸኛል… ግን ለዚህም የጊዜ ገደብ አለው። ጊዜ እያለ ነገርን አርግቦ፤ ሃገርን አንድ አርጎ፤ በወያኔ የተሰመረውንና በኦሮሞ ፓለቲከኞች ያለ ልክ የተለጠጠውን የጎሳ ፓለቲካ ንዶ፤ ሰው በሰውነቱ ተመዝኖ በሃገሪቱ አራት ማዕዘን ሰርቶ የሚኖርባት ምድር ለማየት እንናፍቃለን። ሌላው ሁሉ ልብ ውልቅ ነው። የውሃ ወቀጣ ፓለቲካ! በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share