April 4, 2023
5 mins read

የአብይ የጎርጎራው ጉዞ ሽፋን ናት – መሳይ መኮነን

Gorgora ጎርጎራ 1 3
#image_title

ዓላማው የኦሮሚያ ብልጽግናን የእውር ድንብር ሽምጥ ግልቢያ አሜን ብላችሁ ተቀበሉ ዓይነት መዳረሻው የሆነ ጥብቅ ውይይት ለማድረግ ነው። ሰውዬው የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም ውስጥ ዘው ብሎ ገብተው እየተንቦራጨቁ ነው። በመላው ኦሮሚያ ሰልፍ አስወጥተው እሳቸው ባህር ዳር ላይ ”እንግዲህ በኦሮሞ ዓይን ከመጣችሁ ጫፌን መንካት ትችላላችሁ። እኔ ተነካሁ ማለት ይህ የምታዩት ማዕበል ፋሲል ቤተመንግስት ለመድረስ 24 ሰዓት አይፈጅበትም” የምትል ፍርሃት ወለድ ማስፈራሪያ ለማሰማት ተዘጋጅተዋል። እያበቃ ያለው ሳምንት የሰውዬውን እውነተኛ ቀለም ከምን ጊዜውም በላይ ፍንትው አድርጎ አውጥቷል። ጭምብላቸው ወልቆ የተደበቀው ማንነታቸው ዕርቃኑን አደባባይ ላይ ተሰጥቷል። በተለይ ”እኛ ኦሮሞዎች ኢትዮጵያን አናፈርስም። ማፍረስ ከፈለግን ደግሞ የሚያቆመን ሃይል የለም” የሚል ንግግር በፓርላማ ካሰሙ በኋላ አንደኛውን በስብሰናል፡ ዶፍ በሆነ ዝናብ ውስጥም መራመድ እንችላለን እያሉ ናቸው።

እነጌታቸው ረዳ ያልተቀደሰው ጋብቻ ላይ ከታደሙና ጫጉላ ሽርሽሯንም ከአቶ ሽመልስ ጋር ካሳለፉ በኋላ ወደ መቀሌ ተመለሰዋል። በዚህ ሳምንት የሁለት ዓመቷን በጀት ከድጎማዋ ጋር ይልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠ/ሚሩ ባህርዳር ላይ የአማራ አመራሮችን በስብሰባ ሲጠምዱ የእሳቸው የነፍስ አጋር፡ የሚስጢራዊ ፕሮጀክቶች ተባባሪ አዘጋጅ የሆኑት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ደግሞ ከህወሀት ጋር የተጀመረውን ልዩ ግንኙነት መልክ በማስያዝ ላይ እረፍት አጥተው ሰንብተዋል። የባህርዳሩም ሆነ የአዲስ አበባው የሁለቱ የኦሮሚያ ብልጽግና መሪዎች ዓላማ ከዚህ በፊት እንደነበረው ኮንቪንስ ወይም ኮንፊውዝ አይደለም። ዓይን ያወጣ የበላይነት ጥማችንን ከዳር ለማድረስ በጀመርነው ጎዳና ላይ እንቅፋት አትሁኑብን የሚል ግብና ተልዕኮ ያለው ነው። እንቅፋት ከሆናችሁ ሀገሪቱን ”ዝናብ ያበላሸው ሰርግ” እናስመስላታለን የምትልም ማስፈራሪያ ታክሎበታል።

ጠ/ሚሩ ጓዛቸውን ጠቅልለው የጎሳ ፖሊቲካ ውስጥ ከገቡ ሰነባብተዋል። ሰሞኑን ‘ምን ታመጣላችሁ’ ብለው በአደባባይ ስለማን እስከቀራኒዮ ድረስ እንደሚዋደቁ በግልጽ ነግረውናል። ከዚህ በኋላ እሳቸውን የኢትዮጵያ ዋስና ጠበቃ አድርጎ የሚያምን ሰው ካለ ጤንነቱን በጊዜ ይፈትሽ። የነገውን ሰልፍ ሲያስጠሩ ዓላማው ግልጽ ነው። እኔ የምሞትለትና ለእኔ የሚሞትልኝ ብሄር አለኝ ነው መልዕክቱ። በበቀደሙ የፓርላማ ውሏአቸው ‘ስልጣን ልቀቅ’ ተባልኩኝ ብለው በንዴት ጦፈው፡ እጅግ አሳፋሪ የሆነ የፊዚክስ (እሳቸው የማቲማቲክስ ቢሉትም’) ቲዮሪ አንስተው ፡የብሄር ካርድ በመምዘዝ ሲጫወቱ ቀጣዩ አካሄዳቸው ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አይከብድም ነበር።

ሰውዬው አሁን ፍጥነት ላይ ናቸው። ፍሬን የበጠሰ መኪና ሆነዋል። በግንድም፡ በድንጋይም፡ ብቻ በሆነ ሃይል ማስቆም ካልተቻለ በዚህ ፍጥነታቸው የሚያደርሱት ጉዳት በቀላሉ የሚቀለበስ ላይሆን ይችላል። ችኩልነት + ሴራ + ጥራዝ ነጠቅ እውቀት + ዘረኝነት + የአቅም ማነስ + ስልጣን ተደማምረው ተነስተዋል። ፊት ለፊት ያገኘውን ሁሉ እየጠረማመሰ ነው። ገደሉ ሩቅ አይደለም። ፍሬን የበጠሰው መኪና ግስጋሴው ወደዚያው ነው። በቶሎ የምናስቆመው እንዴት ነው? የሚለው አብዝቶ የሚያስጨንቀን፡ የጊዜው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው።

 

Gorgora (ጎርጎራ)|Amhara Region (አማራ)|City Gallery

https://www.skyscrapercity.com/threads/gorgora-%E1%8C%8E%E1%88%AD%E1%8C%8E%E1%88%AB-amhara-region-%E1%8A%A0%E1%88%9B%E1%88%AB-city-gallery.1075467/

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop