March 12, 2023
2 mins read

በሀገራችን የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት መዳበር አስፈላጊ መሆኑን በጽኑ ያምናል – ኢዜማ

ezema 1 2emaለዚህ ሥርዓት መዳበር ዋና ሚና ከሚጫወቱት ተቋማት መካከል የፖለቲካ ፓርቲዎች ተጠቃሽ ናቸው። እነዚህ ፓርቲዎች የሀገሪቱን ሕጎች አክብረው በሰላማዊ መንገድ እስከተንቀሳቀሱ ድረስ ማንም አካል በሐይል እንቅስቃሴያቸውን ሊያስቆም አይገባም።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተመለከትነው እንዳለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ጉባዔዎቻቸውን እንዳያደርጉ እየተከለከሉ ይገኛሉ። ለአብነትም የካቲት 26/2015 ዓ.ም እናት ፓርቲ እንዲሁም በዛሬው ዕለት መጋቢት 03/2015 ዓ.ም የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ጉባኤ እንዳያደርጉ ክልከላ ተደርጎባቸዋል።

ይኽ ተግባር የመድብለ ፓርቲ ሥርዓትን ለማምጣት የሚደረገውን ጥረት የሚያከስም ዓይን ያወጣ ህገ ወጥ ተግባር በመሆኑ የመንግስትን ድርጊት በጽኑ እናወግዛለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መሠል ድርጊቶችን ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት የምንረዳ ቢሆንም የችግሩን ልክ በሚመጥን መልኩ ሐላፊነቱን እንዲወጣ እንጠይቃለን።

በተጨማሪም በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የመንግስት የፀጥታ ሐይሎች በሕግ ከተሰጣቸው ስልጣን በመተላለፍ እንዲህ አይነት ሕገወጥ ድርጊቶችን ባለመፈፀም ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መዳበር ገለልተኛ ተቋምነታቸውን እንዲያረጋግጡ ጥሪ እናቀርባለን።

እንዲህ አይነት ሕገወጥ ተግባር ሲፈጸም ምንም እንዳልተፈጠረ የምትመለከቱ የመንግስት አካላት እና የሕዝብ መገናኛ ብዙሃን በዝምታ የድርጊቱ ተባባሪ መሆናችሁን እናሳውቃለን።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሕዝብ ግንኙነት

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው እና አሁን ላይ በአማራ ፋኖ በጎጃም የሁለተኛ (ተፈራ ) ክፍለጦር ሰብሳቢ የነበረው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ በክብር ተሰዋ። የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህሎና አደጋ ለመቀልበስ ያለ

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሐዘን መግለጫ ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል !

January 22, 2025
ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

Go toTop