March 11, 2023
11 mins read

እንደ ጺላጦስ እጅን ታጥቦ ከወንጀል ንፁህ ለመሆን መሞከር ያስተዛዝባል ! – ተዘራ አሰጉ ከምድረ እንግሊዝ

331766965 764234115335124 319202604788453992 n 1 1

የዲያስፓራ የብልፅግና ተለጣፊዎችና የለገሰ ቱሉ ተብየ የማናለብኝነት የንቀትና የይስሙላ የቁራ ጩህት መግለጫዎች ገዳዮች ፣ አፈናቃዮች እና ግፈኞች ከደሙ ንፁህ መስለው በስልጣን ይዘልቁ ዘንድ ማህበረሰቡን የሚያዘናጉበት ስልት ብልፅግናዎች ከሕውሃት አባታቸው የወረሱትና የኮረጀት ባህሪና እካሄድ መሆኑ ግልፅና ግልፅ ነው።

ሕውሃት በ997ቱ ምርጫ ወቅት በመላ ሃገረቱ በተለይ በመዲናዋ አዲስ አበባ በአብላጫ ድምፅ ሲሸነፍ “የመራጮች የሕዝብ ድምፅ የይከበር የአደባባይ ነውጥን ለማፈን ያደረገው ጭፍጨፋና የአሮሞ ብልፅግና በአሁኑ ስዓት እያከናወነ ያለው የኢትዮጵያና የአማራ ጠል ገዳይኑቱ ፣ ወደ እስር ማጋዙና የመሰሬነት ባህሪዎች በአብዛኛው ተመሳሳይነት አላቸው።

አምላክ በአምሳሉ የፈጠረውን የሰው ልጅ ሞት ፣ ስቃይ ፣ መከራ ፣ መፈናቀል ወ.ዘ.ተ. በይቅርታ ፣ በካሳ ፣ በገንዘብና በንዋይ ተምኖ ለማወራረድ መሞከር ለአንዳንዶቹ እሽርጋጅ ባንዳዎች ፣ ተከፋዮችና ወጭት ሰባሪዎች የሚመስላቸው ከአለቆቻቸው ድግስ ቤት ታድሞ ውስኪ እና ቁርጥ እንደማወራረድ ነው።

ትዝ ይለኛል ህወሃት በ1997 ምርጫ ከሁለት መቶ በላይ ንፁሃንን በአዲስ አበባ ከተማ ሲጨፈጭፍ የአሁኖቹ “የተግባር ምክር ቤት ፣ Defend Ethiopia ፣ በእየ ኢምባሲው ተሰግስገው እሁን የሚያነፈንፉ ውሻ ደም ላሾች ፣ የብልፅግና መንግስት ጋሻጃግሬዎችና ተከፋዮች የአምናዎቹ ቅንጅቶችና ግንቦቴዎች ” የያኔውን ዐይን ያወጣ ግድያና ጭካኔ “ተመጣጣኝ ነው ወይስ ተመጣጣኝ አይደለም” እያሉ በህውሃት ደባዊ ትርክት ጀሮአችን ያደነቀሩና አጀንዳ ተቀብለው ያራግቡ እንደነበር የአደባባይ ሚስጥር ነው።

ያኔ በውይይቱ የታደሙ ወገኖች “በሃገራችን ፍትሃ ነገስት ፣ ዘመናዊ ሕግና ቱፊት” መሰረት” አንድ መርፌ የሰረቀና እንድ በሬ ሰርቆ የነዳ ያው ወንጀለኛ ነው ” የሚል የሕግን ጠርዝን ተከትለው ለማስረዳት ሞክረው ነበር ፣ ግን ማን ሰምቶ።

የሕግን አግባቦት የማይረዳ ፣ በትምህርት ቤት ደጅ ያላለፈ የመንደር አውደልዳይ ሲናገርም ፣ ሲዳፈርም ፣ ሲከትብም በሌላ ጠርዝ ያለውን የተጎዳ ወገን ስሜት አይረዳም።

ምክንያቱም “ውሻ በበላበት ይጮሃል” እንዲሉ የአዛዦቻቸሁንና የጌቶቻችሁን መዳኛ መንገድ ፣ የስልጣን ዘመን ማረዘሚያና መሰንበቻ ስለምትናፍቁና ስለምትሹ የማወናበጃ ፣ የመሸንገያ ፣ መንግስት መልካም ተናገራችሁ እንዲላቸሁ ፣ ድጋፋዊ መግለጫ ሰጡ ተብላችሁ መንግስት ነጥብ እንዲቆጥረላችሁ በሚል መናኛ የሽንገላ ስራ መስራታችሁ አመላቸሁና የለመዳችሁ አባዚያቸው ስለሆነ “ኧረ ተው ፣ ይበቃል” ከማለት በቀር ምን እንበላቸሁ ፣ ማፈሪያዎች።

ለኢትዮጵያ ህዝብ ባህዳን የሆኑት የተባበሩት መንግስታት ፣ አለም አቀፍ የፍትህና ፍርድ ፅህፈት ቤት /International court of justice”፣ የአውሮፓ ህብረት ና አለም አቀፍ ተቋማት ወ.ዘ.ተ. የብልፅግና መንግስት ያደረሳቸውን ዘር የማጥፋት ክዋኔዎች በአግባቡ ተጣርተው ፍርድ ይሰጥ ዘንድ እየተከራከሩ ባሉበት ወቅት “የእናት ልጅ ዥንጉርጉር” እንዲሉ ከእኛው አብራክ የተፈራችሁ የህንግዲህ ልጆችና ልወደድ ባዮች ፍሬፈርሲኪ የሆነ ደብዳቤ በመፃፍና መግለጫ በመስጠት እምቢ ባዮን ሕዝብ ሊታደናግሩና ግራ ሊታጋቡ በየፊናቸው በመሯሯጥ መሆናችሁ ትንሽነታችሁን ያሳያል።

ሌላው ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የተጎዱትን ማቋቋም ፣ መርዳትና መደገፍ እንጂ ፖለቲካ ውስጥ ገብቶ መዘንቆልና መዳከር ምን የሚሉት ነው።

የረቀቀውን የመንግስት ደባ በጎረሱት ድጎማ ፣ ጉርሻና ፍርፋሪ ተገፋፍተው የተገፋውን ሕዝብ የደምና የሙት ገላን ሽጠው ሌላ ተጨማሪ መሃያ ለማወራረድ መኳተናቸው ያሳዝናል ፣ እነደዚህ ሆኖ ከሰውነት ጎዳና መውጣት ያንገሸግሻል።

በተጎዳ ጎን ፣ ነፍስ ፣ ስጋ ፣ ሞራልና መንፈስ እሳት ፣ እረመጥና ስይፍ መሸንቆር ምን የሚሉት ነው ፣ ኧረ እፈሩ ።

እነዚህ የሃሳብ ፣ የአመለካከት ፣ የእውቀትና የጥበብ ድውያን የሆኑ “እዛኝ ቅቤ አንጓቾች ” ሊገነዘቡት የሚገባው አንኳር ገዳይ ወንጀል የፈፀመው የመንግስት አካልና ለወንጀሉ መፈፀም የገንዘብ ፣ የሃሳብ ግፊት እና ድጋፍ በማከናወን የመንግስት ጀሮና ዐይን ለአለፉት አምስት ዓመታት እንዲደፈን ፣ እንዲደናበርና መንግስት ተብየው እንደልቡ ሕዝብን ፣ የሃይማኖት ተቋማትንና መሰሎችን በግፍ እንዲገል ፣ እንዲያሰቃይ ፣ ወደ እስር ቤት እንዲያግዝ፣ እንዲያዋርድ ወ.ዘ.ተ. የራሳቸሁን ሚና ስለተጫወታችሁና አስተዋፅኦ በማበርከታቸው እንዲሀም በወገኖቻችን ላይ በተለይ በወለጋ ፣ በአጣየ ፣ በቤንሻንጉል ፣ በደቡብና በመላ ኢትዮጵያ ለተፈፀመው ወንጀል እጃቸው እንዳለበት ስለሚታወቅ ጊዜ ሲመጣና ነፃነት ሲታወጅ ዋጋ እንደምትከፍሉ ልትገነዘቡ ይገባል እንላለን።

ሕዝብ ነቅቶ ፣ በቃ ብሎና ታግሎ መከራና ሞቱን እንዳያስቆም የማዘናጋት ስራ ስለሰራችሁ “እንደጺላጦስ” እጃቸውን ታጠባችሁ ከወንጅሉ ነፃ ነን ልትሉ አንደማይቻላችሁ ልትገነዘቡ ይገባል እንላችዋለን።

ህሊናቸው እያርበተበታቸው ፣ እየሸነቆጣቸው ፣ ቅር ቅር እያላቸሁና ቁራሽ የጣለላችሁ መንግስት እንዳይነካ ፣ እድሜው እንዲራዘም በሚል ፈሊጣዊ ዘይቤ እንደዚህ አይነት በደም የተቀላ የሚያንገሸግሽ “የቁራ ጨኅት” የመሰለ የሽንገላ ፅሁፍ መፃፋችሁና መልእክት በዚህ የመከራ ወቅት ማስተላለፋቸሁ ባይገርመንም አካሄዳቸው በጣም ያስተዛዝባል።

ምን አለበት በሰለጠነው ዓለም እየኖራችሁ ስራቸውን እየሰራችሀ ሕይወታሁን ቢትገፉ ፣ ካልሆነ የትግሉን ስልት ስላላወቃችሁት ” ራስ ሳይጠና ጉተና” እንዱሉ ዝም ማለትን ማንን ገደለ ።

ቢያንስ ቢያንስ በዚህ ሰዓት የኢትዮጵያ ሕዝብ “የሎሄ የሎሄ” እያለ ” ወይ ውረድ ወይ ፍረድ” እያለ ወደ አምላኩ እያንጋጠጠ ባለበት ሰዓት የተሰጣችሁን የአቃጣሪነት መንዳ እየቆረጠማችሁ በመኖር ፋንታ መዘላበድና መዘላበድና “እንደ እከካም አህያ” በገዳይ ትክሻ ጎን መታከክ ምን ይፈይዳል። ታዘብናችሁ እናንተ ከሞቱት በላይ ፣ ካሉት በታች ናችሁ እንላለን ደጋግመን።

በየስርዓቱ “አለን ፣ አለን እና እኛ ያላቦካነው ሊጥ አይጋገርም አላችሁሳ” ጃል ፣ በቃችሁ። ትግሉን ለፋኖ ፣ ለዘርማና ለተተኪው ወጣት ትውልድ ስጡት እንላለን። እነ “እምቢ አላረጅም” ሙሽርናና ፖለቲከኛነት እኮ የዕድሜ ገደብ አለው።

በቃ ፣ በቃ ፣ በቃ ” ሲበዛ እኮ ማርም ይገለማል ። ሞት እኮ የገበጣ ጭዋታ አይደለም ። ወይ ነዶ ዘንድሮ ፣ በስንቱ እርር ፣ ድብን እንበል ፣ ቁስላችን እስኪ ሽርና ለበደላችን አግባብ ያለው ፍትህና መልስ እስክናገኝ ድረስ ከፊታችን ዞር በሉልን እባካችሁ እንላለን።

ተዘራ አሰጉ

ከምድረ እንግሊዝ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop