February 8, 2023
17 mins read

 በሤጣን ፈረሥ እየጋለቡ ግፍ መሥራትን የተዋህዶ ልጆች ይቃወማሉ

 በሤጣን ፈረሥ እየጋለቡ ግፍ መሥራትን የተዋህዶ ልጆች ይቃወማሉ ። ያውም እንደ አቡነ ጴጥሮስ በመሰዋትነት ።

 ጮራ እንዲሆነን ይኽንን ግጥም ከባለቅኔው ተዋስኩ ።

( ወልደ  ትንሣኤ ፤ የክርስትና ሥሜ ነው ። ሃሌሉያ )

       እንደሰዶም

ሞኝ አንግስ ተግቶ እንደሰከረ ፤ ፍቶት አናቱ ላይ ወጥቶ

የሚያደርገውን አሳጥቶ

ያለአባት አዳሩ ሲያወራጨው

መለኮት መቅሰፍት አውርዶ ፣ የሰው ልጅ በንፍር ውሃ

ሟምቶ ሲቀልጥ እንደ ጨው

የነገሩ ምላሽ የጥፋቱ ቁርሿ ፣ የቅጣቱ ውርጅብኝ …

ሂድበት ነው ሂጂብኝ

በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ምኑም ምናምኑም እየተወተፈ

ንውር እንደጓሮ አይደርቄ ጎመን ፣ ባዋጅ እየተከተፈ

አለም በቃኝ በራሱ ፈርዶ

ከፈንኳ ሳይበቃ ፤ መቀመቅ ገባ ተዋርዶ

ምን ግድ አለው ፣ ዲበ ኩሉ ፣ የፍትህ አምላክ እንጂ እሱ

ለሰውማ ራሱ ነው ዋሱ …ልቡ ያመለከተውነው ፣ ምሱ

ለአብነት አነሳሁት እንጂ ሰዶምና ጎሞራን

ጉዳዬ ከሰሜን ተራራ ልጆች ነው

እንድርጭት በስለው ፣ እንደባጩት ተሰደው

ያስከበሩት ደን አሞራን

ከጀምበር  መፍለቂያ ከፅዮን

ከቅኔ ቤት መሪጌታ …ኤዶንን እንደመቀነት

እሰከአቀፋት ግቢ አግዶ ጊዮን …

አለት እንደ በቆሎ እሸት ፈልፍለው

ቤተ መቅደሳቸውን ንሰው

በፍቅርና በትህትና ተጋርተው

ሞኝ ባያፍር ዘመዱ ያፍር ብለው

ቁልቁል እንደ ጅራተፍየል ፣ ይጠበቃል ማዕረጉ …

ነገርን በወግ መርምሮ

ቢሆን ሎሚ ለሁለት አስታርቆ

እንደ እራስ ፈርዶ…በቃ ጠብ በቃ ብሎ

በሃሌ በማሳረጉ እንጂ…

ዳኛ ፊት ማን ያደርገው ነበር ባለሟል

ለሱእንጂ ሰግሮ ሰማ  ችሎት  ፣ ለሱእንጂ ለማ ተሰይሟል

ከሳሽና ተከሳሽማ ግራና ቀኝ ነው መቆሚያቸው

ምሶሰው … ቢሻው ከጭንቅ ሊያወጣ

ቢሻው ሊያዳፍን …ምሶ ነው ።

ብቻ በቃን ፤

ኢትዮጵያ እጆቿን የዘረጋችው ዛሬ ነው

ሌላም ጊዜ ከአምላኳ ጎን አትለይም

የአሁኑ ግን ቁርጥ ነው

የትውልድ ጥንድ ምጥ ነው ።

ሞት አንገት ላይ ደረሰ …ማህተምን ሊፈታተን

እኛው ቤት እምቦሳ ብለን ያደምነው

እልፍኛችንን ከፍተን

……………………..

ገፅ ( 58  _59 )

ይኽንን የባለቅኔውን የሙሉጌታ ተስፋዬን ( ኢትዮጵያዊ ሊቅ ) ግጥም  ለአንባቢ ሳቀርብ ፣ የዘመኑ ፖለቲኮኞቻችን ፣ ይልቁኑም አንዳንድ ፣ የአበልፃጊው መንግስት  ፣ በተዋረድ ያሉ ህግ አስፈፃሚዎች ፣ በሤጣን ፈረስ የሚጋልቡ በመሆናቸው  ፤ ይህ ድርጊት የሶዶምና የጎሞራ ሰዎች ድርጊት መሆኑንን ለማሳሰብ ነው ። እነዚህን ሐጢያተኛ እና ወንጀለኛ   ግለሰቦች ገዢው ፖርቲ በጊዜ   ገለል   እስካላደረጋቸው ድረስ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ጨምሮ ፣ ዜጎች በአጠቃላይ  ፣ ሽንት ቤት ውስጥ ከተሰቃዩት አባት የባሰ ውርደት እንደሚያጋጥመን ፤ እየተቀጣጠለ ያለውን እሣት አሥተውለን በቀላሉ መረዳት አያዳግተንም ።

መንግስት ውስጥ ያሉ ፣ ፈሪሃ እግዛብሔር ያላቸው ባለሥልጣናት ( በሲቪሉም በወታደሩም )   በተረጋጋ አእምሮ  እዛም ቤት እሣት እንዳለ ተረድተው ግን ፣ ዛሬ መላውን ኦሮሚያን የወረሯት ሤጣናት  እጃቸውን ከጥፋት  በአፋጣኝ እንዲሰበስብ ካለደረጉ እነሱም የሎጥን ሚስት እጣ ፈንታ ያገኛሉ ። የሐጢያቱ ተባባሪነታቸውን በተግባር አስመስክረዋልና !..

የህዝቡን አንድነት በኃይል እየናዱ “ አንድነት ፖርክ “ በማለት አራት ኪሎ ላይ ታላቅ የቱሪስት መሥህብ የሆነ ሥፍራ መገንባት ፤ “ የወዳጅነት አደባባይ “ በማለት ሰው የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ በመፈቃቀር እንዲኖር እንፈልጋለን ማለት ፣ በተግባር ግን አባቶቻችን በደምና በአጥንታቸው የገነቧትን መናድ ፤  “ እዛም ቤት ያለው እሣት በሌሎች ላይ ጉዳት እንዲያደርስ መገፋፋት ነው ። ይኽ ደግሞ የሞኝ ድርጊት ነው ። በእሣት የሚጫወት ብልህ የለምና ! ደግሞም ፣  በአጋጣሚ በኮስ አበደች  ፖለቲካ ፣ ሥልጣን እንዳገኛችሁ ና በመልካም አንደበታችሁ ፣ በቃላችሁ የዜጎችን ይሁንታ እንዳገኛችሁ አትዘንጉ ።  በህዝቡ ውስጥ እልፍ ባለአእምሮዎች እንዳሉም ተረዱ ። በማሰበ ፣ በዕውቀት ፣ በችሎታ ፣ በሥርዓት ፣ በጨዋነት ሺ ጊዜ የሚያስከነዷችሁ በህዝብ ውስጥ አሉ ። ውሸት ይብቃችሁ ።  አገር መውደድ ፣ ዜጎችን በማክበር በተግባር  የሚገለጥ እንጂ ቋንቋን በማምለክ በቃላት የሚታይ እውነት አይሆንም ።  እምነትም ቁርኝቱ ከሁሉን ቻዩ አምላክ ጋራ እንጂ ከቋንቋ  ጋር አይደለም ።  እግዚአብሔር ለቋንቋ ና ለነገድ አይገደውም ። እግዛብሔር  የሚገደው በአምሳያው ለፈጠረው ሰው ሁሉ ነው ። ቀይ ፣ ጥቁር ፣ ነጭ ፣ ቢጫ  ፣ጥይም መልክ ይኑረው ፤ ኦሮሞ ፣ አማራ ፣ ትግሬ ፣ ሱማሌ  ወዘተ ።  ” ነኝ  ፤ ብሎ ቢገበዝም ፣ ቅጣቱ የናቡከደናፆር አይነት እንደሚሆን ከወዲሁ እወቁ ። በእናንተ ባይደርስ በልጆቻችሁና በልጅ ልጆቻችሁ እንደሚደርስ እወቁ ። ሁላችንም የእግዚአብሔር የእጁ ሥራ ነን ። በእግዛብሔር ፊትም ሁላችንም እኩል እንደሆንን ኢየሱስ ክርስቶስ በወጉ አስተምሮናል ።

ይኽንን የኃይማኖት አውነት የኃይማኖት ትምህርት ማስተማሪያ ኮሌጅ ውስጥ  ገብቶ ያልተማረ ህኖም ግን ከህፃንነቱ ጀምሮ  በክርስቶስ  ሥቅለት ፣ ሞት እና ትንሣኤ … በብሉይ ኪዳን እና  በሐዲስ ኪዳን ትምህርት ቤተ ክርስቲያን በመመላለስ፣ አእምሮውን ያበለፀገና ቀፈጣሪው ፍቅር የበለፀገ አእምሮ ያለው  ሁሉ  ጠንቅቆ ያውቃል ።

እንሆ ዛሬ ይኽንን ጠንካራ እምነታችንን ለማስካድ ፣ ሤጣን  አንገታችን ለማነቅ እየተገዳደረን ነው ።  …ማህተባችንን ለማስወለቅ እየተናነቀን ነው ። ሰዶምን እንዳንሆን  ግን የሰዶማውያንን  ፀያፍ እምነት በብርቱ ልንዋጋ ና ልጆቻችንን ከጥቃቱ ልንከላከል ይገባናል ። ይኽ ግጥም የዛሬውን ዱብ ዕዳ ፣ ከትላንቱ የመቅሰፍት ዱብዳ ጋር ያመሳሰለ ነው ።

 

ሙሉጌታ ተስፋዬ  ” የባለቅኔ ምህላ ” በተሰኘ የግጥም መፀሐፉ ፣ ለዛሬና ለነገው ትውልድ የሚበጅ ዕውቀት ፣ ትቷልን አልፏል ። በንፁህ ልቡም በገነት ይኖራል።  ሙሉጌታ ተስፋዬ ፣ ለኢትዮጵያዊያን የኢትዮጵያዊነትን ሥሜት በልባቸው ለማበልፀግ የሚበቃ ጥበብን የተጎናፀፈ ባለቅኔ ነው ። …

ሙሉጌታ ተስፋዬ ( ጀግና ባለቅኔያችን ) ለኢትዮጵያዊያን ፣ ቅኔያዊ መልዕክቱ ፣  ዛሬ በእጅጉ ያስፈልገናል ።  አዎ ፣ እምነታችን በመናፍቃን የተደፈረበት ፣ አብያተ ክርስቲያናችን ቅጥር ውስጥ መፀሐፍ ቅዱስ የያዙ ክርስቲያኖች በሴጣን ደማቸው እንደጎርፍ የፈሰሰበት  እጅግ አሳዛኝና አሳፋሪ ጊዜ ላይ ደርሰናል  ። ይኽ የሚጠቁመን ምድራችን በከፊል እንደሰዶምና ገሞራ አይነት ሰዎች መሞላቷን ነው ። ለስጋቸው እንጂ ለነፍሳቸው ደንታ በሌላቸው ።

ዓለምን የፈጠራት መድሃኒዓለምን የካዱ ፣ ምንም አያመጣም ያሉ ፣  በመሳሪያ ( በሴጣን ኃይል ) ታጅበው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ሊያፈርሱ ብቻ ሳይሆን ክርስትናንን ዓለማዊ ለማድረግ ተነስተዋል ክርስትና የመጣው ከፈጣሪያችን ነው ።   ለክርስትናችን ለክራችን ለማተማችን ደስ እያለን እንሞታለን ። ትላንት አቡነ ጴጥሮስ ደስ እያላቸው ሞተዋል  ። ከሳቸው በኋላም በመላው ኢትዮጵያ ሥለ ክርስቶስ ፍቅር በፋሺሽስቶች የተገደሉ  መሰዋት የሆኑ በሺ የሚቆጠሩ ናቸው ።

ለመሆኑ ለአምሥት አመቱ ተጋድሎ እና ለነፃነታችን ፋና ወጊ የሆኑት ፣ ዋና ተዋንያን  ፣ በዛን ዘመን ፣ ህዘበ ክርስቲያኑ ለፋሺስቱ የኢጣሊያን መንግስት እንዳይገዛ ገዝተው ፣ በኢጣሊያን  መትረየስ የተሰው ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ  አቡነ ጴጥሮስ አይደሉምን ? ( የታላቁን ደራሲ ና በለቅኔ የሎሬት  የፀጋዬ ገ/ መድህንን “ ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት ግጥም ያነቧል ። )

የዛሬ ባለሥልጣን ሁሉ ሟች እና ኃላፊ ነው  ። ከሞት አያመልጥም ። ጥይት ባይገለው ፣ ባዮሎጂ ወይም ድንገተኛ አደጋ ይገለዋል ። እንደ ሁሉም ሰው   ባለሥልጣናትም ሆኑ ኃያለን ነን  ባዮች  በጊዜያቸው ከዚች ምድር ይሰናበታሉ ። ዛሬ በሥሜት ወይም በብሽቅ ፖለቲካ ጠላቴ ያልከውን ሥለገደልክ ሞት ለአንተ የሚቀርልህ እንዳይመስልህ ! ሞት   ሁሌም በህይወት ካለ ሰው ጋራ የሚጎዝ ነው ። … ፈጣሪ በቃ ሲለን እስትንፋሳችን ይቋረጣል ።

ይህ እውነት ቢሆንም እውነቱን ለመቀበል የታወሩ  ፣  የፈጣሪያችንን ኃያልነት የካዱ ፣  ፕለቲካውን ለማጦዝ እንደቻልነው ፣  ሰማያዊውን መንግሥት እናጦዘዋለን ብለው የሚያስቡ ( ልክ እንደሴጣን )   በዚች ቅድስት አገር ዛሬና አሁን ለፈጣሪዋ ለመድሃኒዓለም ባደረችው ቤተክርስቲያን ጉያ ውስጥ መፈጠራቸው  በእጅጉ ያሳዝናል ።  ሰው ዓለም በቃኝ ብሎ እንዴት የዓለም ና የሥጋ ፍቃዱን ለማሳካት ጦር ይሰብቃል ? ያውም ፀረ ክርስቶስ በሆነው ማርክሳዊ ህሳቤ ውስጥ ተወሽቆ ?!

በእውነቱ ፕለቲከኞቹ ሳይሆኑ የክርስቶስ ልጆች የሆኑ ፣ ሆኖም ግን በሥጋ ምኞት ተጠልፈው ፣ ሥጋ ና ክፉ መሻቱ አሸንፏቸው ፣ ከእዚህ ዓለም ገዢ ጋር ተባብረው ለመስራት የወሰኑ ከቤተክርስቲያኗ ያፈነገጡ አባቶች ናቸው ጥፈተኞች  ። እነዚህ ጥፋተኝች ላይ አንድ የሆነችሁ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውግዘት ማስተላለፏ ይታወቃል ። ክህነታቸውን ገፋ አቶ እንዲሰኙ አውጃለች ። እነዚህ አቶዎች ዛሬም አባት ነን ብለው እየተንቀሳቀሱ ነው ።  ያውም  በዓለማዊ ፖለቲከኞች ታጅበው ። ይኽ  የሚያመለክተን በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደው ፖለታካ ማበዱን ነው ። ፖለቲካ የግለሰቦችን መብት ማስከበሪያ እንጃ   መጨቋኛ መሣሪያ ያለመሆኑ ይታወቃል ። መንግሥትም ሞራል ያለው እንዲሆን የፖለቲካ ሣይንቲስቶች ከጥንት ጀምረው መክረዋል ።  ፖለቲከኞቻችን ፣  በራሳቸው ላይ ሊደረግ የማይፈቅዱትን  ፣ “ ሥልጣን በእጃችን ነው ። “ በማለት ግፍ ባይሰሩና ጡር ለልጆቻቸው ባያቆዩ መልካም ነው ። ደግሞም በእሣት መጫወት ደጋፊ አያስገኝም ። እሣት ፣ እሣት ጫሪውን እንኳ አይምርምና ! በእሣት  መጫወት  አገርን ያፈርሳል  እንጂ አይገነባም ።

1 Comment

  1. ገና ሳትወለድ ነፍስህ ተቅበዝብዛ
    እግር አፈራርቀህ ሩጫ ብታበዛ
    በባትሪ ፈልገህ ከአረብ ከፈረንጆች
    ቱርክም ውስጥ ብታስስ የግራኝን ወዳጆች
    ሮማም ብትሻገር
    ሙሶሎኒ ሀገር
    ማኔ ቴቄል ፋሬስ ተብሎ ያንተ ነገር
    እህል ውሃህ አልቋል
    ሸምበቆህም ወድቋል
    በመሣሪያ ብዛት
    በተክንኮልም ክፋት
    በሠራዊትም ቁጥር አትድንም ከጥፋት።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

329734453 724680935705099 1995416846987077594 n 1
Previous Story

የሻሸመኔ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩት ቄስ ሀረገወይን አርፈዋል፡

325882562 690540682797922 6769289718252856093 n 2
Next Story

በደም የጨቀዬው የሳሪዮስ መስቀል

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop