February 8, 2023
2 mins read

በደም የጨቀዬው የሳሪዮስ መስቀል

 

በደም የጨቀዬው የሳሪዮስ መስቀል፣

ባልነበር ልዩነት ባልተሰራ በደል፣

መንጋውን ሰብስቦ ይላል እንበቀል።

የኦነግ ሲኖዶስ የጨበጠው መስቀል፣

ይላል ግደል!ግደል! ይላል ስቀል!ስቀል!

ከፍ ካለው ቦታ እራሱን አውርዶ፣

ቀሳውስቱን ገሎ ፣ምዕመናኑን አርዶ፣

ክርስቲያን ነኝ ይላል ክርስትናን ክዶ፣

የት ይሆን መድረሻው ከቶ ሄዶ ሄዶ?

መንበሩን እረግጦ ቤተስኪያን አርክሶ፣

ጽላቱን ወርውሮ፣ተቋሙን አፍርሶ፣

አትግደል ያለውን ትዕዛዙን ጥሶ፣

ሌላ ጽላት ይዟል በሰው ደም ለውሶ።

እኔስ አዘንኩለት ለኦሮሞ መንጋ፣

ሃይማኖቱን ጥሎ ሃይማኖት ፍለጋ፣

ለባእዳን እምነት እጁን ሲዘረጋ፣

እርስ በርሱ ሲላጋ፣ ሲጋደል ሲዋጋ።

ምን ይሰማው ይሆን አዚሙ ሲለቀው፣

ይኸ ጊዜ አልፎ ሲገፈፍ  ጨለማው፣

ብርሃን ሲፈነጥቅ ሌሊቱ ሲነጋ፣

ከልጅ ልጆቹ ጋር ቁጭ ብሎ ሲያወጋ ?

የእብሪቱ ክምር እንደ እምቧይ ይናዳል፣

በታሪክ ሚዛን ላይ ትውልዱ ይፈርዳል፣

የጊዜ ጉዳይ ነው!

ሁሉም ሳይደበቅ ፊት ለፊት ይወጣል፣

ማቅ አልባሽ ማቅ ለብሶ ሃዘን ይቀመጣል።

አጋጣሚ ሆኖ በቦታው  ባልገኝ፣

አሁን ግን እላለሁ እኔ እሱን አያርገኝ።

አገሬ አዲስ

የካቲት 1 ቀን 2015 ዓም(08-02-20230

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop