በደም የጨቀዬው የሳሪዮስ መስቀል

 

በደም የጨቀዬው የሳሪዮስ መስቀል፣

ባልነበር ልዩነት ባልተሰራ በደል፣

መንጋውን ሰብስቦ ይላል እንበቀል።

የኦነግ ሲኖዶስ የጨበጠው መስቀል፣

ይላል ግደል!ግደል! ይላል ስቀል!ስቀል!

ከፍ ካለው ቦታ እራሱን አውርዶ፣

ቀሳውስቱን ገሎ ፣ምዕመናኑን አርዶ፣

ክርስቲያን ነኝ ይላል ክርስትናን ክዶ፣

የት ይሆን መድረሻው ከቶ ሄዶ ሄዶ?

መንበሩን እረግጦ ቤተስኪያን አርክሶ፣

ጽላቱን ወርውሮ፣ተቋሙን አፍርሶ፣

አትግደል ያለውን ትዕዛዙን ጥሶ፣

ሌላ ጽላት ይዟል በሰው ደም ለውሶ።

እኔስ አዘንኩለት ለኦሮሞ መንጋ፣

ሃይማኖቱን ጥሎ ሃይማኖት ፍለጋ፣

ለባእዳን እምነት እጁን ሲዘረጋ፣

እርስ በርሱ ሲላጋ፣ ሲጋደል ሲዋጋ።

ምን ይሰማው ይሆን አዚሙ ሲለቀው፣

ይኸ ጊዜ አልፎ ሲገፈፍ  ጨለማው፣

ብርሃን ሲፈነጥቅ ሌሊቱ ሲነጋ፣

ከልጅ ልጆቹ ጋር ቁጭ ብሎ ሲያወጋ ?

የእብሪቱ ክምር እንደ እምቧይ ይናዳል፣

በታሪክ ሚዛን ላይ ትውልዱ ይፈርዳል፣

የጊዜ ጉዳይ ነው!

ሁሉም ሳይደበቅ ፊት ለፊት ይወጣል፣

ማቅ አልባሽ ማቅ ለብሶ ሃዘን ይቀመጣል።

አጋጣሚ ሆኖ በቦታው  ባልገኝ፣

አሁን ግን እላለሁ እኔ እሱን አያርገኝ።

አገሬ አዲስ

የካቲት 1 ቀን 2015 ዓም(08-02-20230

 

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ““ነጻ”” ይወጣ ይሆን? ( ከአሁንገና ዓለማየሁ)

3 Comments

  1. ከሳርዮስ በላይ ጁዋር መሃመድ፤መራራ ጉዲና ነው የባሱብን እስላሙ ጁዋር ለኦሮሞዎች ጳጳስ ሲመርጥላቸው የዚህን ምስጢር አእምሮ ያለው ይመርምረው፡፡

  2. ጎበዝ እኝህ ሰውየ ተጠልፈው ሊሆን ይችላል እስቲ እናግኛቸው መረጃዎች ታግተው ነው ይላሉ እንሱን ሽፋን ተጠቀሙ እንጂ ጳጳስና አቡኑ ሽመልስና አብይ ጁዋር ናቸው ይባላል

  3. “የሻሸመኔ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩት ቄስ ሀረገወይን አርፈዋል” አቶ አካለ ወልድ በዚህ አሳዛኝ ሞት ምን ይሰማዎታል? ከጁዋርና ኦሮሙማ ትእዛዝ ባይቀበሉ የኝህ ካህን ነብስ ባልተቀጠፈ ነበር በመሰርቱ ከጁዋር ይልቅ እሳቸው ይቀርቦት ነበር ጁዋር ክርስቲያኑን በሜንጫ ግደሉ ሲል እኝህ ሰው ግን የሱን ሃሳብ አይጋሩም ነበር፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share