December 18, 2022
2 mins read

እናንተ ፈስኩ! – በላይነህ አባተ

Abiy a killer

ነፋስና ጊዜ በበልጉ ዘርቷችሁ፣
እንደ ባድማ አረም ያገፈገፋችሁ፣
ይሁና ዘር አጥፉ እየተሻማችሁ፣
ብርቱ ክንድ መንግሎ እንሰተሚነቅላችሁ፡፡

ዘራቸው ተቆጥሮ ድሆች ይጨፍጨፉ፣
ዘር አይጥፋ ያሉ ወህኒ ይታጎሩ፣
እናንተ ለድግስ ሂዱ ተሰብሰቡ፣
ሆድን አስፍታችሁ ዛቁ ብሉ ጠጡ፡፡

ሕፃናት እናቶች የእንባ ጎርፍ ያፍስሱ፣
እናንተ ዶልቱ ገልፍጡና ሳቁ፣
የብርቱካን ውሀ ጨምቃችሁ ሰርብቁ፣
ጠጅ በብርሌ ብርዙንም ጨልጡ፣
ደም እንደሆነ ግን ጭራሽ እንዳትረሱ፡፡

ምዕመናን ታቦት ውስጥ መስጊድ ይቃጠሉ፣
እናንተ ግን በሱፍ ከራባት ታነቁ፣
ቁማርን ተንኮልን እንዳምናው ዶልቱ፣
እንደ በፊቶች መቃብር እስክትገቡ፣
አፈርና ትቢያ አመድ እስክትሆኑ፡፡

እንደ ዘመሚቶች እንደ ቅንቡርሶቹ፣
የሰማእት ሥጋን አጥንትን ቆርጥሙ፣
እንደ እምቧይ አብጣችሁ እስከምትፈርጡ፡፡

የፀደቀ የለም ውስዶ የእግዜርን ነፍስ፣
ተነቅሎ ይሞታል ይሸታል እንደ እርኩስ፣
ልክ እንደ ይሁዳ እንደነ ጲላጦስ፡፡

ያ ጊዜ እስኪመጣ እናንተ ፈስኩ፣
እናቶቹ ታርደው ህፃናት ሲያለቅሱ፣
አዛውንት ተሰደው መንገድ ዳር ሲተኙ፣
ፍትህ የጠየቁ ወህኒ ወርደው ሲያድሩ፡፡

እናንተ ፈስኩ!

በላይነህ አባተ ([email protected])
ታህሳስ ሁለት ሺ አስራ አምስት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop