December 4, 2022
8 mins read

ፓትሪያሪክና ጳጳሳት ሆይ!

መቼ ይሆን እንደ አቡነ ጴጥሮስና አቡነ ሚካኤል “ከምዕመና በፊት እኛን መስዋእት አድርጉ ምድሪቷም ለጭራቆች አትገዥ!” ብለው የሚገዝቱ አባቶች የምናየው?

ጳጳስ ሆይ ሕዝብ ታለቀ እንኳን አማኝ መሐራና ደመወዝስ ይኖራል ወይ?

synod 2 1

በላይነህ አባተ ([email protected])

ፓትሪያሪክና ጳጳሳት ሆይ! በአለፉት ሰላሳ አንድ ዓመታት ሕዝብ እየተጨፈጨፈ እናንተ የቤተክርስቲያኗን ቋንጃ ልሰብር መጣሁ ያለውን ይህ አድግን እየተከተላችሁ ስለልማት ስትደሰኩሩ፣  በአስር ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በየጊዜው እየተሰደዱ መኝታቸው ጪንጫ መሬት ትራሳቸው ድንጋይ ሲሆን እናንተ ትንቡክ ተሚል ፍራሻችሁ እንቅልፋቸውን ስትለጥጡ እንደኖራችሁ ይታወቃል፡፡ በተለይ ባለፉት አራት ዓመታት ደመወዛችሁን የሚከፍሉት ምዕመናን አንገታቸው ሲቀሉና የእምነት ሥፍራዎች ባለቤት እንደሌለው ጫካ ሲቃጠሉ ተፎቃችሁ ተንፈላሳችሁ መኖርን እንደቀጠላችሁ መለኮትም ሕዝብም ያውቃል፡፡

ሮጠው ያልጠገቡ ልጃገረዶች በጭራቆች ታግተው በሚሰቃዩበት ሰዓት እናንተ በታገቱት ልጃገረዶች ስለት ፍትፍታቸውን እየበላችሁና በሽንጣም መኪና እየተሽከረከራችሁ አለማችሁን መቅጨት ቀጠላችሁ፡፡ አሁንም ከበፊቱም የከፋ አገር በእሳት እየነደደ ህፃን፣ እርጉዝ፣ አሮጊትና ወጣቶች  በገጀራ ሲቀሉ፣ በጦር ሲወጉ፣ በባሩድ ሲረግፉና መጤ እየተባሉ በላያቸው ቤታቸው ሲቃጠል አፋችሁን ምዕመናን በሚጋግሩት ዳቦና በሚሰሩት ዶሮ ወጥ ጠቅጥቃችሁ ዝም አላችሁ፡፡

መጽሐፉ እስተንፋስ ያለው ሁሉ እንዲተነፍስ ያዝዛል፡፡ ዳሩ ግን እናንተ ይህንን የመጽሐፍ ቃል በመሻር በመላ አገሪቱ የሰው ልጅ ደም እንደ ጅረት ሲፈስ እናንተ እንኳን እንደነ አቡነ ጴጥሮስ ራሳችሁን ለመስዋእትነት ልታቀርቡ ያላዬ ያልሰማ መስላችሁ ተስገብግቦ ባቄላ እንደ ዋጠ አውራ ዶሮ ጪጪ ብላችኋል፡፡

ለክርስትናና ለፍትህ ሲሉ ተዘቅዝቀው የታረዱትንና የተሰቃዩትን ሐዋርያት ስም ጴጥሮስን፣ ጳውሎስን፣ ማርቆስን፣ ሉቃስን፣ ዮሐንስን፣ ቴዎፍሎስን፣ ማትያስን፣ ገብርዔልን፣ ቀውስጦስን፣ ገሪማን ወዘተርፈ ወርሳችሁ እናንተ እነሱን ታሰቃዩአቸውና ታረዷቸው ጪራቆች ጋር ቆማችሁ ስትታዘዙ ይታያል፡፡ አቡነ ጴጥሮስና አቡነ ሚካዔል የጨበጡትን መቋሚያ እየጎተታችሁ የሞሶሎኒን የአላማ ዲቃላዎችን ተከትላችኋል፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ አቡነ ጎርጎሪዎስና መላከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ የጣፏችውን መጽሐፍት እያገላበጣችሁና በቆሙበት መንበር ተገትራችሁ ለከሀዲ ገዥዎች “የልማት” ካድሬ ሆናችሁ ስትታዘዙና ስታገለግሉ ይስተዋላል፡፡

አንዳንዶቻችሁ እንዲያውም መጻሕፍተ መነኮሳት መነኩሴ ከገንዘብ በጣም ይራቅ የሚለውን ሕግ ሽራችሁ ከአገር ውስጥና በውጭ አገር ታሉ ቤተክርስቲያናትም ደመወዝ እየተቀበላችሁ በመክበር የክርስቶስንና የሐዋሪያቱን ተቃራኒ መንገድ በመከተል ላይ እንዳላችሁ በእግዜርም ሆነ በሕዝብ ደጅ ይታወቃል፡፡

ፓትሪያሪክና ጳጳሳት ሆይ! በስግብግብነት፣ በራስ ወዳድነት፣ በሆዳምነትና በፍርሃት የሚቀልቧችሁን በጎቻችሁን ለቀበሮ ገብራችሁ ወደ እማይቀረው ዓለም ስትሄዱ የሰማዩን ዳኛ ምን ሰርተን መጣን ልትሉት ነው?

“የእምነት ቦታ እየተቀጣለ ምእመናን ሲደደዱና በገጀራ ሲቀሉ እናንተ እነሱን ለማዳን እንደ ጳውሎስና ጴጥሮስ መስዋእት እንድትሆኑ ቤተክርስትያን አደራ ስትጥልባችሁ ድምጣችሁን አጥፍታችሁ ክትፏችሁንና ቁርጣችሁን ትዝቁ ነበር” ብሎ መለኮት ሲያፋጥጣችሁ ምን ልትመልሱ ነው?

“ልጃገረዶች ከትምህርት ቤት ተጠልፈው ሲሰቃዩና ወላጆቻቸውም የምድር ሲዖል ሲኖሩ እናንተ እነሱ ልጆቻቸውን እንዲመልስላቸው ያስገቡትን ስለት እየዋጣችሁ በምቾት ኑሯችሁን ትቀጩ ነበር” ብሎ ተሚዛን ሲያስቀምጣችሁ ምን ሊውጣችሁ ነው?

ሥራ የሌለው እምነት የሞተ ነው የሚለውን ጠቅሶ “የጨበጣችሁትን መስቀል፣ የደፋችሁትን ቆብ፣ የደረባችሁት ካባና የተሸከማችሁትን የሐዋርያትና የቅዱሳን ስም በምን ሥራ ተረጎማችሁት?” ብሎ ቢጠይቃችሁ በምን ግብር ተረጎምነው ልትሉት ነው?

ታሪክስ “በእናንተ ዘመን ምእመናን እንደ በግ በካራ ሲታረዱ፣ የክርስቶስ ማደሪያ ቤተክርስትያኖች ባለቤት እንዳጣ ጫካ በአሪዎሶች ሲቃጠሉ እናንተ ፓትሪያሪኮችና  ጳጳሳት ምንም ሳታደርጉ ጪጪ ብላችሁ ሆዳቸውን እየሞላችሁ በምእመናን አስራት በተገነባ የአማረ ህንፃ ውስጥ ትንቡክ በሚል አልጋ ስትንፈላሰሱ ታድሩ ነበር” እያለ በጦር እየወጋችሁ ሲኖር ህመሙን እንዴት ልትችሉት ነው?

ፓትሪያሪክና ጳጳሳት ሆይ! “በጎቻችሁን ለቀበሮ፣ ቤተክርስትያናችሁን ለእሳት ገብራችሁ ወደ እማይቀረው ዓለም

ስትጠሩ የሰማዩን ዳኛ ምን ሰርተን መጣን ትሉት ይሆን? እስከምትጠሩ ሂሳቡን እምነታችሁን ክፉኛ እንደ ጦር ለወጋው ሥጋችሁ ብታሰሉትስ ሕዝቡ ታለቀ እንኳን አማኝ መሐራና ደመዎዝስ ይኖራል ወይ?

መቼ ይሆን እንደ አቡነ ጴጥሮስና አቡነ ሚካኤል ህፃናትን፣ እርጉዞችን፣ አቅመ ደካሞችንና ሌላውንም ከመግደልህ በፊት እኔን ሰዋ መሬቷም ለጭራቆች አትገዥ ብሎ የሚገዝት የሃይማኖት አባት የምናየው?

መጀመርያ ሐምሌ ሁለት ሺ አስራ ሁለት ዓ.ም. እንደገና ህዳር አስራ አምስት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም   January 10, 2025  በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና

በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡

January 10, 2025
Go toTop