የሰሜኑ ጦርነት እና ድርድር|Prosperity | Amhara |Fano | Tigray | Abiy Ahmed|

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  አንድነት ፓርቲና 33ቱ ፓርቲዎች በጋራ መስከረም 5 ቀን 2006 በአ.አ ሰላማዊ ሰልፍ ጠሩ (መግለጫውን ይዘናል)

1 Comment

  1. “ደግነቱ ግን የፕሪቶሪያው ስምምነት የተፈረመው የሕወሃት አሸባሪነት ፍረጃ ከመነሳቱ በፊት በመሆኑ ሰራ ፈጻሚው አካል የተወካዩች ምክር ቤት ፍረጃውን ሳያነሳለት በርሱ ፍላጎት ያደረገው ስልሆነ በህግ ከተሰጠው ስልጣን በላይ ሄዷል። ስለሆነም ተፈጻሚነቱ ህጋዊነት ይጎድለዋል።”

    ከፍ ብሎ ያስፈርኩትን በሚመለከት ማብራሪያ ለጠየቃችሁኝ መልሴ ከታች መልሴ ከታች ሰፍሯል።

    የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣ አዋጅ – አዋጅ ቁጥር ፩ሺ፩፻፸፮፨፪ሺ፲፪

    ሙሉው አዋጅ ይኀው ፡ https://www.lawethiopia.com/images/latest%20proclamations/1176%20A%20PROCLAMATION%20TO%20PROVIDE%20FOR%20THE%20PREVENTION%20AND%20SUPPRESSION%20OF%20TERRORISM%20CRIMES.pdf

    ለምንነጋገርበት ጉዳይ አግባብነት ያላችው አንቀጾች ፡

    አንቀጽ ፲፰ – ድርጅትን በአሸባሪነት የመሰየም ሥልጣን

    ፩- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብር ወንጀል ውስጥ የተሳተፈ ድርጅትን በአሸባሪነት ለመሰየም ይችላል፡፡

    ፳ – የውሳኔ ሀሳብ አቀራረብ ሥነ ሥርዓት

    ፪ – የሚኒስትሮች ምክር ቤት በፌደራል ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ የቀረበውን በአሸባሪነት የመሰየም የውሳኔ ሀሳብ ሲያጸድቀው ለህዝብ ተወካዮችምክር ቤት ያቀርባል፡፡

    ፳፪ – በአሸባሪነት የመሰየም ውጤት

    ፩ – በዚህ አዋጅ መሰረት በአሸባሪነት የተሰየመ ድርጅት ስያሜው ተፈጻሚ ከሚሆንበት ጊዜ ጀምሮ የሚያደርጋቸው ግንኙነቶች እና እንቅስቃሴዎች ህጋዊ ውጤት አይኖራቸውም፡፡

    ፪ – በአሸባሪነት የተሰየመው ድርጅት ህጋዊ ሰውነት ያለው ድርጅት የሆነ እንደሆነ እና በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፯ ንዑስ አንቀጽ (፪) መሠረት በፍርድ ቤት እንዲፈርስ ያልተደረገ እንደሆነ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ድርጅቱ እንዲፈርስ ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ማመልከት አለበት፡፡

    ፫ – በአሸባሪነት የተሰየመ ድርጅት ንብረት በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመንግስት የሚወረስ ይሆናል፡፡ ንብረቱ እንዲወረስ ትዕዛዝ የመስጠት ሂደት ወቅት የሚኖረው ክርክር ድርጅቱ ከመሰየሙ በፊት በቅን ልቦና ከድርጅቱ ጋር ግንኙነት ያደረጉ የሶስተኛ ወገኖችን ጥቅም የተመለከተ ብቻ ይሆናል፡፡

    ፬ የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፫) ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ ከሽብር ወንጀል ጋር የተገናኘ ንብረትን ወይም የአሸባሪ ድርጅትን ንብረት ወይም በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፱ ንዑስ አንቀጽ (፪) መሰረት ንብረቱ የሚወረስ ድርጅትን በሚመለከት የተሻሻለው የፀረሙስና ልዩ የሥነ ሥርአትና የማስረጃ ህግን ጨምሮ ሌሎች ንብረትን ስለመያዝ፣ ስለማገድ ወይም መውረስን የሚመለከቱ ህጎችን መሰረት የሚመራ ይሆናል፡፡

    ፳፬ – ከስያሜ ስለመሰረዝ

    ፩ – የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በአሸባሪነት ተሰይሞ ያለ ድርጅት ስያሜው እንዲሰረዝለት የውሳኔ ሀሳብ ለሚንስትሮች ምክር ቤት ሊያቀርብ ይችላል፤ ምክር ቤቱ የውሳኔ ሀሳቡን ሲቀበለው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል፡፡

    ፪ – የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚኒስትሮች ምክር ቤት የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በመቀበል፤ ከአሸባሪነት ስያሜ ድርጅትን ለመሰረዝ ይችላል፡፡

    ፫ – በዚህ አንቀጽ መሰረት አሸባሪ ድርጅትን ከስያሜ ለመሰረዝ የሚቻለው ድርጅቱ የሽብር ወንጀል መፈጸሙን ያቆመ እና በዚህ ዓይነት ድርጊት ውስጥ ሊሳተፍ የማይችል ስለመሆኑ የታወቀ እንደሆነ ነው፡፡

    ፳፮ – ከስያሜ መሰረዝ ስለሚኖረው ውጤት

    ፩ – የድርጅት የአሸባሪነት ስያሜ መሰረዝ፤

    ከአሸባሪነት መሰረዙ ተፈጻሚ ከሚሆንበት ጊዜ በፊት በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፳፪ መሰረት የተከናወኑ ተግባራት ላይ ምንም ዓይነት ውጤት አይኖረውም፡፡ ስለሆነም የተወረሰ ንብረትን እንዲመለስ መጠየቅን ጨምሮ ያደረጋቸው ግንኙነቶች ህጋዊ ሆነው እንዲቆጠሩ ለመጠየቅ አይችልም፡፡

    ፳፰- ውሳኔን ይፋ ስለማድረግ

    ፩ – የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ድርጅትን በአሸባሪነት ሲሰይም ወይም ከአሸባሪነት ስያሜ ሲሰርዝ፤ ውሳኔውን አገር አቀፍ ተደራሽነት ባለው ጋዜጣ እና ሌላ አግባብነት ባለው የብዙሐን መገናኛ መንገድ ለህዝብ ይፋ ማድረግ አለበት፡፡

    ፪- በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) መሰረት ምክር ቤቱ ይፋ የሚያደርገው ውሳኔ እንዳስፈላጊነቱ ድርጅቱ
    ስለተሰየመበት ምክንያት፣ ስያሜው ተፈጻሚ ስለሚሆንበት ሁኔታ እና መሰል ጉዳዮችን መያዝ አለበት፡፡

    ፳፱ – አሸባሪ ድርጅትን መምራት

    ፩- ማንኛውም ሰው በአሸባሪነት ተሰይሞ ያለን ድርጅት በአጠቃላይ ወይም የድርጅቱን አንድ ክፍል በኃላፊነት የመራ እንደሆነ ድርጅቱን በመምራቱ ብቻ ከሰባት ዓመት እስከ አስራ አምስት ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ይቀጣል፡፡

    ፵፩- የአስፈጻሚ አካላት ተጠያቂነት

    ፩- በዚህ አዋጅ የተመለከተ ወንጀልን የመከላከል፣ የመመርመር ወይም የክርክር ሂደትን የማስፈጸም ኃላፊነት የተሰጠው ማንኛውም ሰው የተሰጠውን ኃላፊነት ህግን በመተላለፍ የፈጸመ እንደሆነ እንደመተላለፉ ዓይነት እና እንዳስከተለው ጉዳት ዓይነት በዲስፕሊን፣ በፍትሐብሔር እና በወንጀል
    ተጠያቂ ይሆናል፡፡

    አንቀጾቹ ግልጽ ናቸው። አስፈላጊ ክሆነ ወደፊት አንቀጽ በ አንቀጽ እመለስበታልሁ።

    እስከዚያው በዚህ ተዝናኑ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share