ማይክ  እና ሐመር – ሲና ዘ ሙሴ

ጥቅምት 24/2013 ዓ/ም  የፈሰሰው የኢትዮጵያ ጀግና ልጆች ደም የፍትህ ያለ ይላል ። እናም ፡-

የማይክን ኃያል ድምፅ ፤

የሐመርን ኃያልነት … ብናውቅም ፤

እጃችን የእሳት ሰደድ ነውና

ፍትህን አስረግጠን

ፈርተን  ዝም አንልም !!

( ሲና ዘ ሙሴ )

“ጦርነት ለወያኔ ዳንስ እንዴት ይሆናል ? ከራስህ አገር ዜጋ ጋር እየተጋደልክ ነው እንዴ ደንስ የሚሆነው ? ይህ ጦርነት እኮ ከውጫ ወራሪዎች ጋር የተደረገ ጦርነት አየደለም ? ” አለች ያቺ ቆንጂዬ ኢትዮጵያዊት ትግራይ ብለው ሰዎች በሰየሙት ክልል የተወለደች የእግዚአብሔር ንፁህ ፍጥረት ። ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እጆን ሰጥታ  ጋዜጠኛ አርያ ተሥፋማርያም  ለጠየቃት ጥያቄ በሠጠችው መልስ  ።

በግድ ፣ በወያኔ ጉልበት ለጦርነት የተሰለፈችው ወጣት ። ጦርነት ዳንስ የሚሆነው ከጠላት ጋር ፣ ከውጪ ወራሪ ጋር ለሀገርህ ሥትዋጋ ብቻ እንደሆነ አሥተምራናለች ። ብራቮ !  “ ንፁሐን እንደ ቅጠል በክላሽና በድሽቃ በሣንጃ እያለቁ ነው እንዴ ? ” ጦርነት የባህል ጫዋታችን ነው ። የምንለወ ? “

ይህ ተደጋግሞ ፣ በገዛ ወንድም ላይ የተፎከረ የወያኔ ካድሬዎች ባዶ ጩኸት ፤ የባዶ በርሜል  ድለቃ ነበር ። እና የገዛ ወገንን ጠልነት ፤ በአቶ  ጌታቸው ረዳ ( ዛሬ ሥራው መርዳት መሆኑ የተገለጠ ። ከከባድ ሚዛኖች ጎን የሚቆም  ። በሞቀበት አፋሽና አጎንባሽ የሚሆን  ። ከአሸናፊው ጎን ተሠልፎ ያሸናፊውን መዝሙር የሚዘምር … መርህ በሌለው ሰው ፣ ተደጋግሞ ሲነገር ነበር።  ከሁሉ የሚያሥቀው ” አብይን ኤርዶጋን አያድነውም ። ሳዳም ሁሴን አያድነውም ። ወዘተ ። ”  ያለው ነበር ። አንድ ጊዜም ተሳስቶ አብይ ፣ አብቹ ። ብሎ እንደነበረ አትዘንጉ ። )

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሕብር ራድዮ ሙሉ ፕሮግራም: የእንግሊዝ መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለማሳፈን በሚሊዮን የሚቆጠር ፓውንድ አውጥቷል የሚል ወቀሳ ቀረበበት.. እና ሌሎችም

ይህንን ፅሑፍ ሥፅፍ የአሥቴርን “ለመድክ ወይ ”  የሚለውን ዘፈን እያዳመጥኩ ነበር ።

” ለመድክ ወይ  ውጩን ከተማ ደጁን …ለመድከው ሁሉን ከተማ ደጁን …ቻለው ወይ ልብህ  …ያማረጥ ጀመረ ልብህ ሌላ  ቆንጆ …አንደበትህ እኔን አሥሮኝ እየዋለ …እንዴት አሥቻለህ ተፈጥሮ …እንደው ትዝ እያለኝ … ” ወዘተ እያለች የምታጎረጉረውን ። እኔም

” ለመድክ ወይ የማይክ እና ሃመርን ነገር

ለመድክ ወይ ማይኩን እና ሃመሩን

ለመድክ ወይ ተግሣፁን እና ኩርኩሙን

ቻለ ወይ ህሊናህ የማይክን ቀጭን ትዕዛዝ …” እላለሁ ።

በእርግጥ የማይክ ሃመር የነገ ግብ የአሜሪካ መንግሥት እና የኢትዮጵያ መንግሥት ያውቁታል ። ከኢትዮጵያ ሠላም ያተርፋሉ ወይስ ያከሥራሉ ? ይህ በሚገባ ተገምግሟል ። አሜሪካንን የሚመሯት አንድ ፐርሰንት የናጠጡ ቱጃሮች  አትራፊ እንደሚሆኑ ባያረጋግጡ ኖሮ ወደዚህ ሠላማዊ መንገድ ህውሃት እንዲመጣ አይፈልጉም ነበር ።

እናም ህውሃትን ከተቀበረበት መቃብር እንዲወጣ አድርገውታል  ። ይህ ሰው በላና የጎደኞቹን አንገት የሚቆርጥ እጅግ ጨካኝ ( ከአይሲስ የከፋ ) ወደ ሥልጣን ከተመለሰ ለትግራይ ህዝብ ዳግም ሞት ነው ። የትህነግ ፖለቲካዊ ሃይማኖት ከአይሲሲመንፈሳዊ ሃይማኖት እጅግ የከፋ ሤጣናዊ ነው ።እናም  በጨካኝነቷ የምትታወቀው ወያኔ ተመልሳ ለሥልጣን ከበቃች  ይህ ለትግራይም ሆነ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሞት ነው ።

ጥንት የፊውዳሎች ጭቆና ባሥመረራቸው   ወያኔ በተባሉ ታጋዮች ሥም የሚጠሩ ሰው በላ ጭራቆች ዳግም ወደ ሥልጣን ወንበር ከተመለሱ ከሞትም ሞትነው ። ዓለም ምንም ፍትህ የሚባል ነገር እንደሌላትም  በዚህ አሥቀያሚ ድርጊት ይገለፃል ። እና ማንም ማይክ እና ሐመር የያዘ ወይም የኒኩለር ጉልበተኛ መንግሥት ፣ ህገወጦችን ፣ ወንጀለኞችን ፣ ንፁሐንን  አራጆችን እየደገፈ ነፃ የሆኑ አገራት መንግሥታትን እያሥፈራራና እጃቸውን እየጠመዘዘ ለድብቁ ብዝበዛው ማመቻቸት እንደሚችል የነቃው ጥቁር ህዝብ ይገነዘባል ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  Video: የእሪታ ቀን፡- ይህ ቪዲዮ ከአንድነት ሰልፍ የተቀነጨበ ሲሆን ሙሉውን ቪዲዮ ከሰዓታት በኋላ እንለቃለን

ዛሬም እነ ማይክ እና ሐመር በንግግራቸው ከፍታ እያሥፈራሩ የአፍሪካን መሪዎች በፈለጉት አቅጣጫ እንዲጓዙ ያሥገድዷቸዋል ። ይህ ግን በኢትዮጵያ እንዲቀጥል ጀግኖች አይፈቅዱም ። የትግራይ ህዝብ ከአንድ ለአምሥት ጥርነፋ መላቀቅ ይገባዋል ። ኢትዮጵያም በካድሬ የማይመራ ፣ በደመነፍሰሰ እና በሥሜት ከጦዘ ኃይማኖታዊ  ፖለቲካ የተፋታ መንግሥት ያሥፈልጋታል   ።

በኢትዮጵያ ውሥጥ ፣  አንድ ሞኝ ሥለጮኸ፣ ሺ ብልጦች አብረውት መጮኽ የለባቸውም ። ሥለሣቀም ፣ ሥለጨፈረም አንዲሁ ። ወይም በተቃራኒው አንድ አሥመሳይ በገሃዱ ዓለም በአደባባይ ሥላለቀሰ  ከእርሱ ጋር ማልቀስ የለባቸውም ። ይህንን ማድረግ የሚቻለው ደግሞ ቆም ብለን ሥናሥብ ነው ።

ቆም ብለን በማሰብ ፣  በዕውቀት ይህንን የሁለት ባለጉዳዮች ( two party’s ) የተሰኘውን የሥምምነት ሰነድ እንፈትሸው  ።  ለመሆኑ የኢትዮጵያን ምርጫ ቦርድ አላውቅም ብሎ ፣ በራሱ ጉልበት በክልሉ ምርጫ ቦርድ አቋቋምኩ ብሎ በጠመንጃው አሥፈራርቶ ከተመረጠና አንገት እየቀላ በማሥፈራራት የትግራይን ክልል በኃይል ከሚያሥተዳድር አረመኔ ጋር ቀድሞውንሥ የአንድ ኩሩ አገር መንግሥት በአንድ ጠረጴዛ ላይ መቀመጥ ነበረበት ወይ ? የሰነዱን ቁንፅል ሃሳብ ብቻ ይፋ በማድረግ ፣ ሙሉውን ሥዕል በመሸፈን ዘላቂ ሠላም ማምጣት ይቻላል ወይ ? ያ ሁሉ መሰዋትነት ከአረመኔ ፣ ከሰው አራጅ እና ለህግ ከማይገዛ ህሊና ቢስ ቡድን ጋር ለመደራደር ነባራዊው ሃቅ  ይፈቅዳል ወይ ?

ኢትዮጵያን  የማይክን ጫጫታ እና የሐማርን ገዳይነት ፈርተን ፍትህ ሥትጨፈለቅ ዝም ብለን እጃችንን አጣምረን ቆመን ማየት አንችልም ።  የራሳችንን ጉዳይ ራሳችን እንፈታለን ። ሥንል ለእኔ ተንበርካኪ አንሆንም ማለት ነው ትርጉሙ ። ጥቅምት 24 ቀን 2013  ዓ/ም ኢትዮጵያን ለገደሉ  ሁሉ መህረት የለም ። ተገቢውን ህጋዊ ቅጣት ማግኘት አለባቸው  ። በኢትዮጵያ አንደራደርም  ። …

ተጨማሪ ያንብቡ:  Hiber Radio: የሕወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ ወታደራዊ ሹም ሶማሊያ ውስጥ በተካሄደ ወታደራዊ ምክክር ላይ እንዳይገኙ ታገዱ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share