October 24, 2022
4 mins read

ዘመን ተሻጋሪና እውነታን መስካሪ የአማራ ህዝብ እንጉርጉሮወች አጭር ቅንጫቢ (እውነቱ ቢሆን)

Amhara

ሀ) ወያኔ የእኔ ናቸው የሚላቸውን በሰሜኑ የአማራ ታሪካዊ ርስቶችና ቦታወች መሆናቸውን  ማረጋገጫ፦

ማረሻው ሚንሽር መጎልጎሊያው ጓንዴ
የአባ ስበር አገር ወልቃይት ጠገዴ

አለማጣ ዉዬ መልሼ አለማጣ
በበሽታዬ ላይ በሽታ ላመጣ

ለ) ጥቃትን በሚመለከት፦

እልም ነው ጭልጥ ነው ዉሀ አይላመጥም
ጠላት ወዳጅ ላይሆን አልለማመጥም

በለው በሚንሽር አስኪደው በዋንዛ
በአባት መሬትና በሚስት የለም ዋዛ

ጠላትማ ምንጊዜም ጠላት ነው
አስቀድሞ መግደል ፊርማቶሪውን ነው

ፊርማቶሪ ማለት ለጠላት የተሸጠ የውስጥ ሰው ማለት ነው፡፡ ይህ አባባል ከራስ ወገን ሆነው በጣሊያን ወረራ ወቅት ለጣልያን ሲሰሩ ለነበሩ የአማራ ባንዳወችና ከሀዲወች በአርበኞች የተገጠመ ግጥም ነው፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁኖቹ የተረኞቹ የኦሮሙማውች አገዛዝ ድረስ ያሉትን ከአማራ ውስጥ ወጥተው አማራን የሚያስጠቁትን ሁሉ ይመለከታል፡፤

በእኛ ዘመንም ይህንኑ ነውረኛ ስራ የሚሰሩትን በተለይም አሁን ላይ ለኦሮሙማ አሽከር ሆነው የአማራ አስጠቂ የሆኑትን የብአደንና የአብን ሆዳሞ አመራሮችን ለይቶ ይመለከታል፡፡ አማራው በአማራነቱ እየታደነ ከማለቁ በፊት አማራውን በተናጠልም ሆነ በጥምረት እየተናበቡ የሚያጠቁትን ጠላቶቹን ማለትም እየተንፈራገጠ ያለውን ወያኔንና በተቃራኒውም እያበጠ ያለውን ኦሮሙማን ስልት ነድፎ ሊያስወግዳቸውና ነጻ ሊሆን የሚችለው አስቀድሞ በውስጡ ያሉትን የአብይ አህመድ ምስለኔወች ሲያስወግድ ብቻና ብቻ ነው፡፡

አማራው አንዲነቱን አጠናክሮና በፋኖ ዙሪያ ተሰባስቦ ቆሞ ሁሉም አማራ በየሰፈሩ፣ በየመንደሩ፣ በየከተማው፣በየወረዳውና በየዞኑ ብሎም በክልል ደረጃ ያሉትን ሆዳሞ የኦሮሙማ ምስለኔወች እየመነጠረ መቀጣጫ በማድረግ ለፋኖ ደጀንነቱን በተግባር ካላረጋገጠ መቼም ቢሆን ከተደገሰለት የኦሮሙማ ወጥመድ አያመልጥም፡፡ እነዚህ የአብይ አህመድ ወደል አህዮች እያሉ አማራ ነጻ ይሆናል ርስቶቹንም ያስመልሳል የፖለቲካ ጥያቀወቹም መልስ ያገኛሉ ማለት ዘበት ነው፡፤

እንድገመው፡፡ አማራ ፍዳውና እዳው ገና እጅግ በጣም ገና ነው፡፡ መፍትሄው ህዝቡን ደጀን ያደረገና ከሆዳሞች የጸዳ የፋኖ(የአማራ ህዝባዊ ሀይል) ትግል ነው፡፡የተግባር ተሳትፎ ነው፡፤ ይህም መደረግ አያለበት ነገ ሳይሆን ዛሬ ነው ; አሁን ነው፡፡ ነገ ይጨልማል፡፤ አማራን ባርያ አድርጎ የሚያስገዛው ወጥመድ በኦሮሙማ ተዘርግቶ አልቋል፡፡ ስለሆነም  ፋኖን አማራው እንደአይነ ብሌኑ ከኦሮሙማና ከምስለኔወቹ ጠብቆ ካላዳነውና ፋኖ ሲመታ ወይንም ትጥቅ እንዲፈታ ሲደረግ ህዝቡ ዝም ካለ  የአማራ ትግል ለረዥም ዘመን ወይንም ጭራሹኑ ተዳፍኖ ሊቀር ይችላል፡፡

 

4 Comments

  1. አማራ እንደ አሁኑ በራሱ ሆዳሞች ሳይታፈን በፊት ጠላቶቹ ሊመሰክሩት የማይፈቅዱት ጀግና ህዝብ ለመሆኑ የዱሮዉን እንተወዉና የትናንትንውን እናስታውስ፡፡
    ከ4 አመት በፊት ወያኔ የሰሜን እዝን በዘር ላይቶና በጨለማ አርዶ ካበቃ በኋላ በዚያው እለት ተግተልትሎ ወደ መሀል አገር እየተመመ የነበረውን የወያኔ የተደራጀ ጦር በቁጥር ትንሽ የሆኑ ነገር ግን በእልህ ውስጣቸው የተቃጠለ የአማራ ልዩ ሀይል አባላት ቅራቅር ላይ ጠብቀው እንዳጨዱትና ወደኋላ አፈግፍጎ እንዲመለስ እንዳደረጉት አይዘነጋም፡፡
    ይህንኑ ታላቅ ገድል የዛሬን አያድርገውና በጊዜው አውሬው ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድ በስም ጭምር ጠርቶ አድንቆ ተናግሯል፡፡ ያኔ ቅራቅር ላይ ወያኔ በቆራጥና ውስታጨው በሲቃ በሚነድ የአማራ ልዩ ሀይል አባላት ባይመታ ኖሮ ታሪክ ተቀይሮ ነበር፡፡ ያ ግትልትል የወያኔ ጦር ይጓዝ የነበረው ከመቀሌ እስከ አራት ኪሎ ባደራው ድርና በጨበጠው የወታደራዊ ደህንነት ኮምፓስ እየተመራ ነበር፡፡ ማከላዊ መንግስት ተብየውም ሆነ የወታደር ደህንነቱ ያኔ ምንም መረጃም ሆነ ዝግጁነት አልነበረውም፡፡
    መታወቅ ያለበት አማራ አሁን በራሱ ሆዳም ሹመኞች ቢታፈንም ወኔው፣ እልሁና በተለይም ዘለአለም የማይሞተው የአማራነት ማንነቱና ነፍጠኛነቱ በውስጡ አለ፡፡ ወደፊትም በጠላቶቹ ላይ ደግሞ ይተገብረዋል!!!

  2. ወያኔና ኦሮሙማሁለቱም የአማራ ጠላቶች ናቸው፤ በተናጠልም ሆነ ሲያስፈልግ እየተናበቡ በጥምረት የአማራን ህዝብ ብዙ ጥቃትና በደል አድረስውበታል፡፡ ህዝቡን አፍኖላቸው አሽከር በሆናቸው በብአደን አማካይነት ጉዳት ማድረሳቸውም ይቀጥላል፡፡ ስልለዚህ አማራ ቀድሞ ማድረግ ያለበት የራሱን ቤት ማጽዳት ነው፡፡ ውስጡን ከሆዳም የአማራ ሹመኞች ካጸዳና በአንዲነት በአማራነቱ ይበልጥ ተደራጅቶ ከቆመ አማራው የውጭ ጠላቶቹን በቀላሉ ይመታቸዋል፡፡

  3. ከላይ በቁጭት ሀሳብ የሰጣችሁ ወገኖች የድርሻችሁን ተወጥታችሁ ከሆነ መልካም ነውና በተረፈ ህይወቱን መተዳደሪያውን ጥሎ ለአማራ የሚማገደውን ግፋ በለው ማለት ብቻ መልካም አይመስልም። ጎበዝ በጣም አሳሳቢ ጉዳይ አሜሪካና የአውሮፓ ህብረት ብድር ድር ካልተገኘን ሙተን እንገኛለን ማለታቸው የጤንነት አይመስልም እነዚህ ከትህነግ በላይ ትህነግ የሆኑት በዚህ ወሳኝ ሁኔታ ካልተገኘን ሲሉ መንግስት መፍቀድ ምን ማለት ነው። ውይይቱ በእንግሊዝኛ የኛ ተደዳሪዎች የድርድሩን ጨብጥ ሊረዱ የሚችሉት አአ ከተመለሱ በሗላ ሰው አንብቦላቸው ነው። ጎበዝ ይሄ ነገር ሶስቴ ሊደገም እንዳይሆን። የመጀመርያው በዳግማዊ ምንሊክ ቆራጥ ውሳኔ በደም ተስተካከለ ሁለተኛው ስዩም መስፍን የተደራደረበት ከመቶ ሽህ በላይ ህይወት ቀጠፈ ቁማሩን ሻቢያ በላው። ድርድሩ ከትግሬዎች ጋር ስለሆነ መደረግ የነበረበት በአማራ መሪነት ግፍ የደረሰበት የአማራ ህዝብ መሆን ነበረበት ተደራዳሪዎቹም ከሀገር ቤት ጄነራል ተፈራ ማሞ፣ አቶ መርሀ ጽድቅ ፣ዶር ደሳለኝ ጫኔ የመሳሰሉ ሲሆኑ ከውጭ ሀገር ዶር አክሎግ ቢራራ፣አቻምየለህ ታምሩ፣ የወልቃይት ኮሚቴና የአማራው መጠቃት ያንገበገባቸውና የአፋር ተዉካዮች ሊሆኑ በተገባ ነበር። ጎበዝ ይህ ካልሆነ ድርድሩ የሚያተኩረው መዳረሻው ለአብይ የተረጋጋ የስልጣን ዘመን ማቆያን ማመቻቸት ነው። እንዴት ነው ይህ ሁሉ ውርጅብኝ የደረሰበት ህዝብ የራሱ ተወካይ የማይኖረው? አማራ የወረቀት ነብር መሆኑን አቁሞ ወደ ተለየ የግል ምእራፍ መድረስ ይገባዋል። በብርሀኑ ነጋ የአማራ ጥላቻ የወደፊቱን ትውልድ ለመቅጣት ከአስር ሽህ በላይ የሆኑ ወጣቶች ፈተና አይቀመጥም ተብሏል የዚህን ውሳኔ ክብደት መገንዘብ ያልቻልን ድንዙዛን ሁነናል። የዚህን ሰውዬ ቢሮ በሰላማዊ ሰልፍ አስጨንቆ ቢሮው ገብቶ ጉሮሮውን አንቆ ማስወጣት በተገባ ነበር። ወንድሞቻችን እስራኤል ውስጥ አድርገውታልና። በተረፈ በዝምታህ ከጸናህ ሽመልስ አብዲሳ፣ጁዋር መሀመድ፣ታዬ ደንዳ ሀጎስ ምንትሴስ ባንተ ስም ይደራደሩሀል።

  4. ፊርማቶሪ የሚለው ቃል አስቆኛል። ያው አማርኛው ከዚህም ከዚያም እንደ ሌላው ቋንቋ ሁሉ ቃል እየተዋሰ ይጠቀማልና የዚህ ቃል መሰረቱ ጣሊያንኛ ይመስለኛል። ግራም ነፈሰ ቀኝ ትርጉም ልክ ነው። እንደዛሬው በሃገራችን የቋንቋ ጦርነት ሳይከፈት ስለ ቋንቋ የተጻፈ አንድ መጽሃፍ አንብቤ ነበር። ቋንቋ በሶስት መንገዶች ያድጋል ይልና በአለም ላይ ያሉ ቋንቋዎች ሁሉ ለመግባቢያነት ይጠቅማሉ ይላል። ቋንቋ የሚያድግበትን ሶስት መንገዶችም ሲጠቁም አዳዲስ ቃላቶችን በመጨመር፤ ነባር ቃላቶችን ትርጉምና አጠቃቀም በመቀየርና ከነጭራሹም ከመዝገበ ቃላቱ በማስወጣት ነው ይላል።
    አማርኛ ቋንቋ የሚያወላዳ ቋንቋ ነው። ለዛ ነው ቀልደኛው አይ አማርኛ እንዳበጅሽ ትበጃለሽ ያለው። በቅኔ፤ በተረትና ምሳሌ፤ በባህላዊ እንጉርጉሮ፤ በግጥም፤ በሰምና ወርቅ ወዘተ ሰው የልቡን በቅርብም በርቀትም ያደርሳል። አንዳንዶች ተጫውተው ከሚያወሩት ጋር ከተለያዪ በህዋላ የጫወታው ትርጉም ዘግይቶ ስለሚገባቸው ምሱን አጥቶ የተቆጣ ባለዛር ይመስል ባዶ ሜዳ ላይ ያዙኝ ልቀቁኝ ለማለት ይከጅላቸዋል። ሶስት ያህል ፈሊጦችን ወይም አባባሎችን ላካፍላችሁና ይብቃኝ።
    ሆዴን እየከፋው ቤት ሥራ ይሉኛል
    አሁን ለሚፈርሰው ምን ያደርግልኛል?

    እንደ ዛሬው ሳይሆን ሸቀጡ ሳይበዛ
    እምዬ ሰቆጣ የነበረሽ ለዛ።

    ሰው በድለን ነበር እኛም እንደ ዋዛ
    ቁናው ቁናችን ነው ትንሹ ዘር በዛ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

negussie
Previous Story

በካናዳ የኦንታሪዎ  ክፍለ ሃገር ለማዘጋጃ ቤት የከንቲባዎችና ካውንስለሮች ሕዝባዊ ምርጫ ትወልደ ኢትይዮጵያዊው  አቶ ንጉሴ ዓዳሙ አሸናፊ ሆነዋል  

177542
Next Story

ይብላን ለዋሸን ሰው ይብላን ለካደን ሰው ! – ተስፋሁን ከበደ ፍራሽ አዳሽ 34 / ጦቢያ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop