July 27, 2022
6 mins read

ንስሐ በሌለበት የሚያርግ ምስጋና የለም – ዓባይነህ ካሤ – ዲን

Abiy 71
ያለፉትን አራት ዓመታት የመራውን ግለሰብ አብይ አህመድን ብንመለከት በሕዝብና በአገር ስም የሚሰጠውንም ሆነ በብድርና በእርዳታ የሚገኘውን ገንዘብ እንደ ግል ሃብቱ ሲበትን፣ለምን  እንዲህ ይሆናል ብለው የጠዬቁትን ምን አገባችሁ እያለ ሲሳደብና ሲያንጓጥጥ ማዬቱ የተለመደ ነው
Abiy 71
ጠሚሩ አሁንም እንደዞረባቸው ሁሉ ላዙርባችሁ አመስጋኝ እንሁን በሚል “ስብከት” ከጠፉበት ተከስተዋል። ፓስተርነታቸው አገርሽቶባቸው ነው የተመለሱት።
ነቢዩ ያለውን ላስታውስ፦
“እጃችሁንም ወደ እኔ ብትዘረጉ ዓይኔን ከእናንተ እሰውራለሁ፥ ልመናንም ብታበዙ አልሰማችሁም፤ እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል። ታጠቡ ሰውነታችሁንም አንጹ፤ የሥራችሁን ክፋት ከዓይኔ ፊት አስወግዱ፤ ክፉ ማድረግን ተዉ፥ መልካም መሥራትን ተማሩ፥ ፍርድን ፈልጉ፥ የተገፋውን አድኑ፥ ለድሀ አደጉ ፍረዱለት ስለ መበለቲቱም ተሟገቱ።” ኢሳ ፩: ፲፭ – ፲፯።
ሌላም ልጨምር
“የሚቃጠለውን መሥዋዕታችሁና የእህሉን ቍርባናችሁን ብታቀርቡልኝም እንኳ አልቀበለውም፤ ለምስጋና መሥዋዕት የምታቀርቡልኝን የሰቡትን እንስሶች አልመለከትም። የዝማሬህንም ጩኸት ከእኔ ዘንድ አርቅ፤ የመሰንቆህንም ዜማ አላደምጥም። ነገር ግን ፍርድ እንደ ውኃ፥ ጽድቅም እንደማይደርቅ ፈሳሽ ይፍሰስ።” አሞ ፭: ፳፪-፳፬።
መጽሐፋችን የሚለው እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ – ከሕፃናት እና ከሚጠቡ አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ ነው። መዝ ፰፡፪። ወዲህም የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ ልብ መንፈስ ነው፤ የተሰበረውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም ይላል። መዝ ፶፡፲፯።
ሲጠቃለል
የኀጥአን መሥዋዕት አስጸያፊ ነው፤ ይልቁንም በክፉ አሳብ ሲያቀርቡት አስጸያፊ ነው። ምሳ ፳፩፡፳፯።
ስለዚህ ጠሚር በአቋራጭ ለመበልጸግ እንዲሚያስቡት በአቋራጭ በእግዚአብሔር ለመሰማት የሚችሉበት ዕድል የለም። ታጠቡ ተብሏል። ዘልሎ ምስጋና የለም። እንዲያው ዙሪያ ጥምጥም ከሚለፉ ንስሐ ይግቡ ንስሐ እንግባ።
እጅዎ ላይ ብዙ ንጹሕ ደም ይጮኻል!!!
————————————————————————–

የአማራ ብልፅግና አመራሮች 6ተኛው የአማራ ክልል ኘሬዝዳንት በመሆን፣ ከኦሮሚያ ብልፅግና ሹመት ለመቀበል እሽቅድምድም ገጥመዋል።” – ፓስተር ደረጀ ከበደ

295238727 2695284933938662 3084026882897880322 n
ፓስተር ደረጀ ከበደ
ፋኖ ሆይ በስምህ ብቻ ጀግና አልልህም። አማራ ሲታረድ የት ነህ? ወንድምህ ሲታፈን የት ነህ? የአማራ ብልፅግና ጥቅምህን አሳልፎ ሲሰጥ አንተ የት ነህ? ፋኖነት መንደር ለመንደር መሳሪያ ተሸክሞ መዞር አይደለም። ድረሱልኝ ለሚሉት አማራዎች መከታ ካልሆንክ፣ በግሌ ፋኖ ብዬ አልጠራህም። አማራን ለመታደግ ባለመስራትህ ቤትህ ድረስ መጥተው እየገደሉህና እያሰሩህ ነው። ዝም ካልክ ገና ይጫወቱብሃል።
ለአመፅ ተነሳ። በወሬ፣ በመግለጫ፣ በስብሰባ፣ ቃለ መጠይቅ ላይ በመንደንፋት ጠላት አይጠፋም። ጠላት የሚብረከረከው በጠንካራ ትግል ብቻ ነው። ውጭ ያለነው በፋይናንስ እንደግፋለን። በእየ ኢንባሲው ድምፅ እንሆናለን። መንግስታትን እናሳምናለን። አገር ቤት ያለኸው ፋኖ ቆርጠህ ውጣ፣ ጭቆናን እምቢ በል። ለወገንህ ለመሞት ጭምር በተግባር አስመስክር።
የፓርላማ ተመራጭ ሆነህ፣ በአብይ አህመድ ደሞዝ እየተከፈለህ እጅህን አውጥተህ ጥያቄ ስለጠየቅክ ጀግና አትባልም። አማራ የሚፈልገው ወንበር ላይ ተቀምጦ የሚደሰኩርለት ሳይሆን፣ መሬት ላይ ታግሎ የሚያታግለው ሰው ነው። ለተጨፈጨፉት አማሮች የህሊና ፆለት ይደረግላቸው፣ ባንዲራ ዝቅ ብሎ ይሰቀል ስላልክ አማራ አይድንም። አብኖች ከዚህ ማደንዘዣ ውጡ።
አዲስ አበባ የሚለው ስሟ ራሱ በቃሬዛ ላይ ነው ያለው። ሁሉንም ጠቀላለው ጨርሰውታል። የአማራ ብልፅግና ነው ፈርሞ የሰጣቸው።
የአማራ ብልፅግና አመራሮች 6ተኛው የአማራ ክልል ኘሬዝዳንት በመሆን፣ ከኦሮሚያ ብልፅግና ሹመት ለመቀበል እሽቅድምድም ገጥመዋል። ጉዳዩ ለተላላኪነት እኔ እበልጥ እኔ በልጥ ሆኗል። የአማራ ጀኖሳይድ፣ የወልቃይት፣ የራያ፣ የአዲስ አበባ ጉዳይ ለእነሱ ምናቸውም አይደለም።

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

296150476 1501522863635041 710486661796228725 n
Previous Story

የኢትዮጵያ ኤንባሲና አየር መንገድ ባልደረቦች ለአትሌቶቻችን በኒው ዋርክ አይሮፕላን ማረፊያ ደማቅ አቀባበልና ሽኝት

294302855 5401020023294611 5806656652684659572 n
Next Story

ፍርድ ቤቱ የታዴዎስ ታንቱን የክስ መቃወሚያ ሳይቀበል ቀረ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop