ሰውዬው (ሀንጌሳ) እውነቱን ተናግሬ ልሙት እያለ ነው። ታዬ ደንዳኣም መጠየቅ ያለባቸው ሰዎች አሉ ብሏል

♦የከተማው ሸኔ አራት ኪሎ ቁጭ ብሎ እያፈነ ይሰውርሃል!!
♦የጫካው ሸኔ እያረደ ይጥልሃል ተናቦ መስራት ይልሃል ይኸው ነው!!


የተከበሩ ዶ/ር ሃንጋሳ ጉዱን ዘረገፉት …

ሰው ማለት ሰው የሚሆን ነው ሰው የጠፋለት
በዚህ ክፉ ሰዓት ትንሽ የተስፋ ጭላልጭል እንዲታየን የሚያደርጉ ሰዎች መኖራቸው የህይወትን ቀጣይነት መኖሩን ያሳየናል…፡፡
ከነዚህ መካከል አንደኛው የተከበሩ ሀንጋሳ አህመድ ኢብራሂም ናቸው…፡፡
የተከበሩ ሀንጋሳ ዛሬ ሁለት ሰዓት በፈጀውና ከ15 ሺህ በላይ ተመልካቾች በተከታተሉት የፌስቡክ የቀጥታ ስርጭት በኦሮምኛ (የተወሰኑ ቁልፍ ነገሮችን ደግሞ በአማርኛ) አስተላልፈዋል…፡፡
በወለጋ የንፁሃንን ጭፍጨፋ እየተፈፀመ ያለው በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዬች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ሃንጋሳ አህመድ ኢብራሂም ተናገሩ አክለውም የኦሮሚያ ፕሬዘዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከስልጣናቸው እንዲነሱ ጠ/ሚ አብይ አህመድን በይፋ በፌስቡክ የቀጥታ ስርጭታቸው ጠይቀዋል …፡፡
ከ 2 ቀናት በፊትም ጠባቂያቸው መገደሉን ተናግረዋል

ያጋለጡት ዋነኛነጥቦች

– አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና እቅድና ተግባር ነው፣
– አብዲ ኢሌ ሲነሳ ሶማሊያ ሰላም እንደሆነው ሁሉ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ በክልሉ ያሉ ባለስልጣናትን እስር ቤት በማስገባት ሰላም ይስፈን፣
– ዶ/ር አብይ ከለማ የቀረበ ወዳጅ አልነበረህም በሱ ላይ የጨከንክ በሽመልስ ላይ መጨከን እንዴት አቃተህ???
– ዶ/ር አብይ የኦሮሚያ ክልልን ካቢኔን አፍርሰህ በአዲስ ተካ፣ ይህንን ካላደረክ አማራ እንዲጨፈጨፍ የምታደርገው አንተ ነህ ወደሚል ድምዳሜ እሄዳለው፣
– እኔ ብሞት እንኳን ወንድሞቼ (አማራ፣ ኦሮሞ፣ ሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች) እውነቱን ስሙ (እወቁት) …።
– ዶ/ር አብይ መሬት ላይ ወርደህ ህዝቡን ይቅርታ ጠይቅ፣ አንተን እና ህዝቡን ለይተው ሊበሉህ ደጅህ ላይ የቆሙ ጅቦች አሉና ቅደማቸው፣
– ዶ/ር አብይ እሰር፣ ቀፍድድ፣ ወስን እና ጨክን፤ አንተን ገለው ቤተመንግስት ሊገቡ ያሰቡ ሰዎች ሰፈራችን ላይ ደርሰዋል (አጃቢዬን ዛሬ ገለውታል ነገ እኔንም ቢገሉኝ እውነት እናገራለሁ) …።
– ኦነግ ለዘመናት ወለጋ ውስጥ ነበር፣ ኦነግ ሀረርጌ እና አርሲ አለ፤ አሁን ኦነግ የመግደያ፣ የመጨፍጨፊያ አቅሙን ከየት አመጣው ብለህ ጠይቅ፤ እኔ ግን እነግርሃለው ሀይሉን እና አቅሙን ያገኘው

ከክልሉ መንግስት ነው…።

– እነ ሽመልስ ዙሪያውን ከበው ሊበሉህ ነው፣ ሊጨርሱህ ነው የመጨረሻው ሰዓት ላይ ደርሰሃል አይንህን ግለጥ ……።
– አማራን ኦሮሚያ ውስጥ መጨፍጨፍ የሚጎዳው ከአማራ ይልቅ ኦሮሞን ነው፣
– የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ስንት ገዳይ እንፈልጋለን፣ ለፍትህ እናቀርባለን ብላችሁ ስንቱን አሳካችሁ፤ ምኑንም አላሳካችሁም ወሬ ብቻ፤ በዚህ መሃል ግን ወንድም እና እህቶቼ (አማራዎች) ወለጋ ውስጥ አለቁ…።
– መቼ ነው ዶ/ር አብይ ከአትክልት ስራ ወጥተህ ጠንከር ያለ ስራ የምትሰራው፤ መቼ ነው የከበበህ መከራ የሚታይህ፣ መቼ ነው ሊበላህ የተነሳው ጅብ የሚታይህ ???!
– ዛሬ አማራን እየገደለ የሚመጣው ሀይል መቆሚያው አንተ ቤት (አራት ኪሎ) ነው …።
– ሽመልስ እና ፍቃዱ ታደሰን ወደ እስር ቤት ካላስገባህ ከዚህ ጥቃት ጀርባ አንተ አለህ ማለት ነው፣
– ለአብዲ ኢሌ ክፍት የሆነ እስር ቤት ለሽመልስ እና ፍቃዱ ዝግ የሆነው ኦሮሞ ስለሆኑ ነው ወይስ አዛዡ አንተ ስለሆንክ??!
– አጉል ጥጋብ እና ሁኔታ ውስጥ ገብታችሁ የአማራን መገደል የምትደግፉ የኦሮሞ ወንድሞቼ እረፉ (ዋ እረፉ ብያለሁ)፣ ነገ ጠዋት አማራ ኦሮሞ ላይ እንዲነሳና እርስ በእርስ እንድንትላለቅ ነው ፍላጎቱ፣

የኦሮሞ ወንድሞቼ ንቁ (በጭራሽ በኦሮሞ ብልጽግና ገመድ እንዳትጠለፉ) …።

– አንተን (አብይን) እያስጠሉ ያሉት ዙሪያህን የከበቡህ እና ሰው ያደረካቸው መናዎች ናቸው …..።
– ኦሮሚያ የሁላችንም ቤት ነው፣ አማራው ተመርጦ ሲታረድ ለምን ካላልን ነገ መከራው በኛና በልጆቻችን ላይ ይደርሳል…።
– ዶ/ር አብይ እስኪ ድንገት ጅማ፣ ሀረርጌ፣ ገራሙለታ፣ አርሲ፣ ወለጋ፣ ባሌ፣ ጭሮ ሂድና ህዝቡን ስማ (መሬት ላይ ያለውን መከራ እይ)፣ ያኔ ምን አይነት የሚመር ዜና እንደምትሰማ እነግርሃለው …።
– የኦሮሞ ካቢቤ ተጠራርጎ እስር ቤት ካልገባና ለፍርድ ካልቀረበ የአማራ መጨፍጨፍም አይቆምም ሀገርም ሰላም አትሆንም!!! ብለዋል…።

አፈትላኪ ዜናዎች

1) የሰሞኑ የአማራ ህፃናት እና እናቶች ጭፍጨፋና መታረድ እራሱ አብይ በደም ፍላት እልቂት ቀስቃሽ የአማራ የጥላቻ ንግግር በማድረግ ነበር::
2) ከዚህ በፊት OBN ብቻ እንዲዘግብ ተደርጎ መተከል ላይ አንድ የአካባቢ “ሽማግሌ” የተባሉ ነገር ግን የክልሉ ም/መሪ የነበረ በኦነግና ህወሃት የአማራ ጥላቻ የተጠመቀ ካድሬ ከ30 ደቂቃ በላይ እልቂት ቀስቃሽ የጥላቻ ንግግር እንዲያደርግ (ቀድሞ በተዘጋጀ መልኩ) አብይ ዝም ብሎ መርዙ እንዲረጭ አደረገ:: ማታውኑ 250 አማራዎች ተጨፈጨፉ:: በጅምላ በዶዘር ተቀበሩ:: አስገዳዩ አብይ አህመድ ነበር::
3) ፓርላማ ላይ ከወሎ-ከሚሴ የተወከሉ ከበቀለ ገሪባና ኃይሉ ጎንፋ የባሱ ኦነጎች የአማራ ፖሊስ ከአማራ ክልል ይውጣልን ብለው በጥላቻ የደም ስራቸው ተወጥሮ እልቂት ቀስቃሽ ንግግር ሲያደርጉ–አብይ እንደፈለጉ እንዲናገሩ አደረገ:: “አማራ ለምን ይጨፈጨፋል” ብለው ያለቀሱ የፓርላማ አባላትን ግን ለፍተኝ ተግሳፅ (ያው ለኡዙ ፓርላማ ትእዛዝ) ሰጠ::
ለ99 ጊዜ:- የአማራ የዘር እልቂት የሚፈፀመው በአብይ አህመድ መሪነት: በኦህዴድና ኦነግ አስፈፃሚነት ነው::

Taye Dendea Aredo 

ተጠያቂነት ይስፈን!
ንፁኃን ዜጎች በግፍ ሲገደሉ የሁሉም ጤነኛ ሰዉ ልብ ያዝናል:: ያዘነ ሀዘኑን መግለፁም አግባብ ይሆናል:: እኛ ደግሞ እንደመንግስት የዜጎችን ደህንነት ማስከበር ትንሹ ኃላፊነታችን ይመስለኛል:: ሰላምና ፀጥታ ከሰፈነ ሌላዉን ህዝቡ ራሱ ይሰረዋል:: ነገር ግን የዜጎች ሞት በየቀኑ ይሰማል:: ግምቢ ላይ የተፈፀመዉን አስነዋሪ ጭፍጨፋ ሳንረሳ ሌላ ጭፍጨፋ በቄለም ዛሬ ተደግሟል:: በነገራችን ላይ ጥፋቱ የማነዉ? ጠያቂና ተጠያቂ ሊኖር ግድ ይላል! ተጠያቂነት ባለመኖሩ አንድ ችግር መቶ ጊዜ ራሱን ይደጋግማል!
በርግጥ ላለፉት ሦስት ዓመታት ኦሮሚያ ላይ የፀጥታ ችግር ገንግኗል:: ከመቼዉም ጊዜ በላይ ህዝባችን እጅግ የከፋ መከራ አይቷል:: እዉነታዉን መናገር ” ስልጣን ፈላጊ” ያስብላል:: እዉነትን ለመደፍጠጥ የስልጣን ልበወለድ ተፅፎ ወደ ላይ ይተረካል:: ለመሆኑ ህዝብ በሌለበት ምድር ስልጣን ለምን ይጠቅማል? አሁን ተጠያቂነትን በማስፈን እንቆቅልሹን መፍታት የህልውና ጉዳይ ሆኗል! ከዚህ ካለፈ አደጋዉ ከቁጥጥር ይወጣል!
ተጨማሪ ያንብቡ:  የዳንኤል ክብረት ጎቤልሳዊ ፍፃሜ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share