ለአፍሪካ ዋናጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ በከፍተኛ የኳስ ብልጫ ግብፅን 2 ለ 0 አሸንፏል

ኢትዮጵያና ግብጽ የአፍሪካ እግር ኳስ ጠንሳሾች ናቸው። ይህን ታሪክ ይጋሩት እንጂ ዛሬ ላይ የሁለቱ አገራት የእግር ኳስ ደረጃ ልዩነቱ ሰፊ ነው።
የደረጃ ልዩነቱ የቱንም ያህል ቢሰፋ ግን በተለያዩ ምክንያቶች የተቀናቃኝነት ስሜታቸው ለአፍታም ደብዝዞ አያውቅም።
ሁለቱ አገራት የአለም ብሎም የአፍሪካ ጥንታዊ ስልጣኔ መገለጫ ከመሆናቸው ባሻገር በተለያዩ የታሪክ አጋጣሚዎች የገጠሙት ጦርነትና የአባይ ወንዝ ትስስር በእግር ኳሱ መንደር ሲገናኙ ፍልሚያቸውን ይበልጥ ያጦዘዋል።
በተለይም ሁለቱ አገራት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታና ውሀ ሙሌት ጋር በተያያዘ ከቅርብ አመታት ወዲህ የገቡበት ውዝግብ ባላንጣነታቸውን አደባባይ እንዳወጣው በርካቶች ይስማሙበታል።
ዋልያዎቹ ከፈርኦኖቹ፣ ሁለቱ አገራት ውጥረት ውስጥ ባሉበት፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታም ተጀምሮ ሶስተኛው ዙር የውሃ ሙሌት ሊከናወን በተቃረበበት በዚህ ወቅት ዛሬ በታላቅ የእግር ኳስ መድረክ ተገናኙ።
በ2023 ኮትዲቯር ለምታዘጋጀው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በማጣሪያ ጨዋታ በምድብ አራት የተደለደሉት ዋልያዎቹና ፈርኦኖቹ በገለልተኛ አገር ማላዊ ላይ ሁለተኛ የምድብ ጨዋታቸውን አከናወኑ።
ብርቅዬዎቹ ዋልያዎችም ያልተጠበቀ ድል በፈርኦኖቹ ላይ ተቀዳጅተው ለሁለቱም አገራት ከእግር ኳስም በላይ ትርጉም ባለው የክብር ፍልሚያ ታሪክ የማይረሳው ገድል ፈጸሙ።
ኢትዮጵያ ይህን ታላቅ ፍልሚያ በሜዳዋ ማስተናገድ አለመቻሏ ቁጭት ውስጥ የከተታቸው ዋልያዎቹ በጄነራላቸው ውበቱ አባተ እየተመሩ በፊት አውራሪዎቹ ዳዋ ሆጤሳና አቡበከር ናስር ቅንጅት የፈርኦኖቹን መረብ ለመድፈር 25 ደቂቃ እንኳን አልፈጀባቸውም።
በታሪክ አጋጣሚ ባለፉት በርካታ አመታት ፈርኦኖቹ ዋልያዎቹን በአስራ አንድ ጨዋታ ሙሉ በሙሉ ማሸነፍ ችለዋል።
ይህም ብቻ ሳይሆን ፈርኦኖቹና ዋልያዎቹ ሲገናኙ ዋልያዎቹ በሰፊ የግብ ልዩነት እንዳይሸነፉ ደጋፊው የሚጨነቅበት ዘመን የሚዘኘጋ አይደለም።
ዛሬ ግን ታሪክ ተቀየረ፣ ዋልያዎቹም ቀንዳቸው መዋጋት ጀመረ። የፈርኦኖቹን መረብ ዳግም ለመድፈር ጨዋታ አቀጣጣዩ ሽመልስ በቀለ ሁለተኛውን አርባ አምስት ደቂቃ መጠበቅ አላስፈለገውም።
ዋልያዎቹ በፍጹም የጨዋታ ብልጫ ፈርኦኖቹ የሚይዙትንና የሚጨብጡትን ሲያሳጡ ሁለቱ አገራት በአፍሪካ እግር ኳስ የደረጃ ሰንጠረዥ ሶስተኛና አርባ ሶስተኛ ላይ የሚገኙ ናቸው ብሎ ለማመን አይቻልም።
ይህን ተአምርና ጣፋጭ ድል ዋልያዎቹ በሜዳቸውና በደጋፊያቸው ፊት ማጣጣም ቢችሉ ምንኛ መልካም ነበር። ሆኖም ይህን ቁጭት ትርጉመ ብዙው ድል አካክሶታል።
ዋልያዎቹ ይህን ታሪክ ለመጻፍ ለአገራቸው ክብር ያላቸውን ሁሉ ሰጥተዋል።
በኢትዮጵያ ስፖርት “ታሪክ ተሰራ” ለአትሌቲክስ ጀግኖች ነበር የሚሰራው። ይህን የዋልያዎቹን ገድል “ታሪክ ተሰራ” ከማለት ውጪ ምን ሊገልጸው ይችላል?።
በቦጋለ አበበ
ETV
——————–
ሰሞኑን ባቀረብነው ጽሑፍ በርካቶች የግብጽ ቡድን በሰፋ የግብ ልዩነት ያሸንፋል ሲሉ ገምተው ነበር። ውጤቱም ኾነ የጨዋታው ብልጫ ግን የተገላቢጦሽ ኾኗል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) በዛሬው ጨዋታ የግብጽን ቡድን በሚገባ በልጠው ታይተዋል።
እሁድ በተከናወነው የመጀመሪያው የአፍሪቃ ዋንጫ የማጣሪያ ግጥሚያ የኢትዮጵያ ቡድን በማላዊ ቡድን የ2 ለ1 ሽንፈት አስተናግዶ ነበር። የዛሬው ድሉ በዋሊያዎቹ ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥሯል።
በሌላ ግጥሚያ ተመሳሳይ ምድብ ውስጥ የሚገኘውየማላዊ ቡድን በጊኒ 1 ለ0 ተሸንፏል። በስታዲየሙ የተገኙ የማላዊ ደጋፊዎች ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ድጋፋቸው ሲገልጡ ታይተዋል። የዋልያዎቹ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከግብጽ ጋር ስለሚኖረው ግጥሚያ ቀደም ሲል ተጠይቀው፦ «የማላዊን ማሸነፍ ተከትሎ የሚገቡ የእነሱ ደጋፊዎቻቸው ከእኛ ጎን ይሆናሉ ብዬ አስባለሁ» ብለው ነበር። ማላዊዎች ኢትዮጵያን በማሸነፋቸው ግብጽ ብትሸነፍ ከምድቡ በነጥብ ከፍ ብሎ ለመገኘት ስለሚረዳቸው ኢትዮጵያን ሊደግፉ ይችላሉ ተብሎ ተገምቶም ነበር።
ለብሔራዊ ቡድናችን በቀጣይ ጨዋታዎችም መልካም እድል እንመኛለን።
ፎቶ፦ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
DW

https://youtu.be/q-LSL5S0kP8

ተጨማሪ ያንብቡ:  Barcelona edges out Manchester United as highest earning team from the 2010-11 Champions League

1 Comment

  1. Well, it is great to hear! Congratulations!
    But it is with a very disturbing mixed feeling I am saying this as we have terribly failed and continued to fail to make our country relatively peaceful and comfortable to live in leave alone making her the champion of peace and free of absolute or abject poverty! And this, I must tell you makes out joy very incomplete because we have lost and keep losing so many values that have been the very sources of our national pride! Real sad!
    Yes, it is the right thing to be proud of registering victory over Egyptian players in this most -liked sport!!!
    But at the end of the day, what matters the most is registering victory over the very overdue political system of horror and total dehumanization orchestrated by a very stupid and ruthless ruling elites of EPRDF/OPDO/Prosperity!
    I hate to say but I have to say that if this generation remains very clumsy or good for nothing about the very essence of how to win freedom, justice, human dignity, and meaningful way of life; it would become and continue to become the very victim of the dirty or very cheap populist political agenda of the ruthless ruing elites and their allies and puppets! And if so, all what is supposed to be the very reason or source of pride including sport and cultural activities will lose their real sense of meaning and value!
    I understand there may be so many compatriots who want to take this very clear and straightforward opinion simply as a matter of politicizing sport or mixing sport with politics. Yes, this criticism would make sense if we were talking about challenges that are expected under a relatively normal circumstance. Sadly enough, our case is incredibly horrible and dehumanizing to the extent of challenging us what we are and who we are? From whom we expect the prevalence of freedom and justice to come?
    Can we claim that we are sportsmen or women and who cares about the reign of horror and devastation? I do not think so! I am not saying stop playing sports or any other activity. Not at all! What I am saying is do not allow yourself to remain under a total political slavery or dehumanization in the name of sport and cultural activist! Make your sports victory complete by fighting hard for freedom and justice both for yourself and your innocent compatriots (people) by telling those stupid and ruthless ruling elites enough is enough!
    I am sorry to say but I have to say that making the flag flew in any sport or any other event and declare victory whereas things inside our own home (country) are extremely embarrassing, dehumanizing, unbearably devastating because of the politically motivated heinous crimes is totally nonsense!
    Our people, unfortunately, have lost their sense of cry and decry leave alone the real sense of enjoying the victory of this or that game!
    If we do not want to badly fool or cheat ourselves, we are in a total delusion (thinking and believing contrary to the very bitter reality on the ground). If you say that this opinion of mine is pessimistic (chelemtegnnet), so be it!
    I want to argue that it is much and much better to recognize and accept what is clear and plain on the ground for so many years and do something about it instead of keep going with the political, moral and social crises we have gone through for so many years, and still keep going with no meaningful end sight or exit! tragic!!!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share