በፖሊስ ይግባኝ የተጠየቀባቸው ተመስገን ደሳለኝ፣ ሰለሞን ሹምዬ እና መዓዛ መሐመድ ከእስር ሳይለቀቁ ቀሩ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ ዋስትና በተፈቀደላቸው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ሰለሞን ሹምዬ እና መዓዛ መሐመድ ላይ ይግባኝ ጠየቀ። የይግባኝ አቤቱታው የቀረበለት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት “ዳኛ የለም” በመባሉ ጉዳዩ ለነገ ረቡዕ ሰኔ 1፤ 2014 ተቀጥሯል።
መርማሪ ፖሊስ ይግባኝ የጠየቀው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሶስቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ የሰጠውን ትዕዛዝ በመቃወም ነው። የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ለጋዜጠኞቹ ዋስትናውን የሰጠው ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 30 ረፋድ በነበረው የችሎት ውሎ ነው።
ፍርድ ቤት ትዕዛዙን ከሰጠ በኋላ የሶስቱም ጋዜጠኞች ቤተሰቦች የተጠየቁትን የዋስትና ገንዘብ መክፈላቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። የፍርድ ቤት መፈቻ ትዕዛዙን ይዘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የተገኙት የሰለሞን ሹምዬ ቤተሰቦች “ይግባኝ ጠይቀናል አንፈታውም” መባላቸውን እህቱ ትግስት ሹምዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግራለች።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት በሚገኘው ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት ሶስቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ዛሬ ከሰዓት በፖሊስ ታጅበው በፍርድ ቤት ቅጽር ግቢ ቢገኙም ችሎት ፊት ሳይቀርቡ ቀርተዋል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ሰራተኞች “የይግባኝ ጉዳይ የሚመለከት ዳኛ የለም” በማለታቸው የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎቹ ታስረው ወደሚገኙበት ፖሊስ ጣቢያ ተመልሰዋል።
(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ተጨማሪ ያንብቡ:  በወልቃይት ምሽግ እየተቆፈረ ነው፣ መሳሪያ እየገባ ነው

1 Comment

  1. What would a generation raised watching Abiy Ahmed’s total disregard for justice and human dignity become? While the public is engulfed in a justified outcry over this shameful injustice and terror, the gamblers in power are busy with other even uglier treasonous acts against the nation.
    Igziabher Libuna YisTen. Kenezihim bandoch yigelaglen.

    Meaze, Solomon and Temesgen are heroes that deserve to be awarded not jailed.

    It is time that a responsible government of the people by the people and for the people be established before these band of unpatriotic spies and cadres totally ruin the future of our children.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share