May 1, 2022
3 mins read

የጎንደር ወጣቶች በአዘዞ አቡበከር ሰዲቅ መስጊድ የዒድ በዓል ማክበሪያ ስፍራን አፀዱ

279657636 5388300227917381 5746710353305444625 n በጎንደር ከሚገኙ ክፍለ ከተሞች አንዷ በሆነችው የአዘዞ ክፍለ ከተማ የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ወጣቶች የተለመደ የዒድ በዓል የፅዳት መርኃ ግብራቸውን በአዘዞ አቡበከር ሰዲቅ መስጊድ በመገኘት አከናውነዋል።
የፅዳት መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት ሰዎች በጎንደር ወንድማማች የክርስትና እና የእስልምና ዕምነት ተከታዮችን ለመነጠል የተሴረው ሴራ ዋጋ የተከፈለበት እና የሚወገዝ ነው ብለዋል።
ይህ የፅንፈኞች ድርጊት ሳይበግረን በዓልን አብረን ለመዋል የተለመደ አብሮነታችን እየተወጣን ነው ሲሉም ተናግረዋል።
የበዓሉ ቀንም ከመስጊድ እስከ ቤት በመገኘት እንደሚያከብሩት ገልፀዋል።
በመስጊዱ ፅዳት መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት አብደላ ኡስማን እና ሐጂ ፈንታሁን አደም ባለፉት ቀናት በጎንደር ሁለቱን እምነቶች አብሮነት ለማጠልሸት የተሠራው ሥራ ያሳዘናቸው መሆኑን ገልጸዋል።
የዒድ በዓል በፀጥታው ስጋት ምክንያት በየዓመቱ ከሚከበርከት አፄ ፋሲል ስታዲየም መካሄዱ ቀርቶ በየመስጊዱ እንዲከበር በመወሰኑ በዓሉ የሚከበርበት መስጊድን ለማፅዳት የክርስቲያን ወንድሞች በመገኘታቸው የተለየ ትርጉም ያለው ነው ሲሉም ተናግረዋል።
የጎንደር ሕዝብ ብዙ የሚፈተን፣ ነገር ግን የማይነጣጠል ወንድማማችነቱን በተግባር ያስመሰከረ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል።
በፅዳቱ የተሳፉ የኅብረተሰብ ክፍሎችም በከተማዋ በተከሰተው የሽብር ሥራ የተሳተፉ ለሰዎች ሕይወት መጥፋት እና ለንብረት መውደም ሴራ የጠነሰሱ እና ያስተባበሩትን በመለየት መንግሥት አስተማሪ እርምጃ እንዲወስድ መጠየቃቸውን ኢብኮ ዘግቧል።
1 ሺሕ 443ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በነገው ዕለት በጎንደር በሁሉም መስጊዶች የዕምነቱ ተከታዮች በተገኙበት ይከበራል።
ሚያዝያ 23/2014
ዋልታ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው እና አሁን ላይ በአማራ ፋኖ በጎጃም የሁለተኛ (ተፈራ ) ክፍለጦር ሰብሳቢ የነበረው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ በክብር ተሰዋ። የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህሎና አደጋ ለመቀልበስ ያለ

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሐዘን መግለጫ ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል !

January 22, 2025
Go toTop