May 1, 2022
3 mins read

የጎንደር ወጣቶች በአዘዞ አቡበከር ሰዲቅ መስጊድ የዒድ በዓል ማክበሪያ ስፍራን አፀዱ

279657636 5388300227917381 5746710353305444625 n
279657636 5388300227917381 5746710353305444625 n በጎንደር ከሚገኙ ክፍለ ከተሞች አንዷ በሆነችው የአዘዞ ክፍለ ከተማ የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ወጣቶች የተለመደ የዒድ በዓል የፅዳት መርኃ ግብራቸውን በአዘዞ አቡበከር ሰዲቅ መስጊድ በመገኘት አከናውነዋል።
የፅዳት መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት ሰዎች በጎንደር ወንድማማች የክርስትና እና የእስልምና ዕምነት ተከታዮችን ለመነጠል የተሴረው ሴራ ዋጋ የተከፈለበት እና የሚወገዝ ነው ብለዋል።
ይህ የፅንፈኞች ድርጊት ሳይበግረን በዓልን አብረን ለመዋል የተለመደ አብሮነታችን እየተወጣን ነው ሲሉም ተናግረዋል።
የበዓሉ ቀንም ከመስጊድ እስከ ቤት በመገኘት እንደሚያከብሩት ገልፀዋል።
በመስጊዱ ፅዳት መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት አብደላ ኡስማን እና ሐጂ ፈንታሁን አደም ባለፉት ቀናት በጎንደር ሁለቱን እምነቶች አብሮነት ለማጠልሸት የተሠራው ሥራ ያሳዘናቸው መሆኑን ገልጸዋል።
የዒድ በዓል በፀጥታው ስጋት ምክንያት በየዓመቱ ከሚከበርከት አፄ ፋሲል ስታዲየም መካሄዱ ቀርቶ በየመስጊዱ እንዲከበር በመወሰኑ በዓሉ የሚከበርበት መስጊድን ለማፅዳት የክርስቲያን ወንድሞች በመገኘታቸው የተለየ ትርጉም ያለው ነው ሲሉም ተናግረዋል።
የጎንደር ሕዝብ ብዙ የሚፈተን፣ ነገር ግን የማይነጣጠል ወንድማማችነቱን በተግባር ያስመሰከረ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል።
በፅዳቱ የተሳፉ የኅብረተሰብ ክፍሎችም በከተማዋ በተከሰተው የሽብር ሥራ የተሳተፉ ለሰዎች ሕይወት መጥፋት እና ለንብረት መውደም ሴራ የጠነሰሱ እና ያስተባበሩትን በመለየት መንግሥት አስተማሪ እርምጃ እንዲወስድ መጠየቃቸውን ኢብኮ ዘግቧል።
1 ሺሕ 443ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በነገው ዕለት በጎንደር በሁሉም መስጊዶች የዕምነቱ ተከታዮች በተገኙበት ይከበራል።
ሚያዝያ 23/2014
ዋልታ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

279262059 535047474890047 3045514952960652307 n
Previous Story

የዐረብ አገሮች በሩሲያና ዩክሬን ላይ ያላቸው የስንዴ ጥገኝነት ዝርዝር ትንታኔ – ጌታቸው ወልዩ (ሜክሲኮ ባህረ-ሰላጤ)

279465543 524124942695360 51720046658015468 n
Next Story

የሀጂ ሙፍቲ መልእክት

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop