April 26, 2022 ዜና 1 min readጎንደር ከተማ ላይ በግፍ የተገደሉት ወንድሞች ቁጥር ሶስት ደርሷል በአሁኑ ሰዓት መስጅዶች እየተደበደቡ ነው፤ የመኖሪያ ቤቶች በጠራራ ፀሃይ እየተዘረፋና የሙስሊሞች ንብረት እየወደመ እንደሆነ ከነዋሪዎቹ ሰምተናል።የክልሉ ለመንግስ አስቸኳይ ምላሽ ካልሰጠ ወይም የፌደራል መንግስት ጣልቃ ገብቶ ካላረጋጋው ጥፋቱ በቀላሉ የሚቆም አይደለም።እባካችሁን ህዝባችን ተጨንቋል።ኃያሉ ጌታችን ሆይ! ተበድለናልና እርዳን።በድሩ ሁሴን Facebook X Pinterest Linkedin Whatsapp Reddit Email 2 Comments ትግሬዎች፤ አህመዲን ጀበል፤ጁዋር መሃመድ፤ኡስታዝ አቡበከር ሎቶሪ ወጣላችሁ ሰውን ስላም አትንሱት ብዙ ቤተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል ተከባብረን እንኑር አታቀጣጥሉት እናንተም የሰራችሁት ማስረጃዉ አለን።Replyእብዶች የራሳቸውን ቤት አቃጥለው ድረሱልን ይላሉ ወይም ዘለው እሳቱ ውስጥ በመግባት አብረው ይነዳሉ። ጎበዝ አብደናል። አሁን ሰው በሃይማኖት ሳቢያ በዚህ ዘመን ይጋጫል? ይህ የሚያሳየው እየቆየን ኋላቀር መሆናችን ነው። የምታመልከው አንድ አምላክ የምትሰበሰብበት ሥፍራ የተለዬ መሆኑ ለብቻው ሰውን እስከ መገዳደል ያደርሳል? ግን ይህ ሁሉ ሸር ሃገርን ለማፍረስ ከታቀደው ሴራ ጋር አብሮ ይሄዳል። ለፈጣሪ ማንም ከማንም የበለጠ ቀናኢ ሊሆን አይችልም። የእስልምና እምነት ቤቶች እየነደድ የእኔ አትንኩ ማለትም አይቻልም። ተያይዞ መጥፋትና መንደድ እንጂ። ሲጀመር ሃይማኖት የሰዎች የማሰሪያ ገመድ ነው። በአስተሳሰብ ያስራል፤ ሰውን ያራርቃል፤ ያቀረበውን ያቀርባል የሚያሳድደውን ያሳድዳል፤ የእኔ እምነት ከአንተ ይሻላል በማለት ይለፋል። ይህ ሁሉ መለፋደድ ነው። የማንም ሃይማኖት፤ ወይም እምነት ከማንም አይበልጥም። እንዴት ባለ ምድር ነው ሰው ለቀብር ወጥቶ እንደ እንስሳ ተራርዶ ለመኖር ቃል የሚግባባው። የዚህ ሁሉ አትራፊ ሟችም ቋሚም አይደለም። የሃገሪቱን እንደ ጧፍ መንደድ የሚሹ የውጭና የውስጥ ሃይሎች እንጂ። ትላንት እልፍ ሰዎች በወለጋ፤ በአርሲ፤ በሃርርና በልዪ ልዪ ሥፍራ ሲታረድና ሲፈናቀሉ ሰላማዊ ሰልፍ ያልወጣው ሃበሻ አሁን ጎንደር ላይ በተጫረው እሳት ሳቢያ የራሳችውንም ለመጫር እንዲመቻቸው ተሰላፊ ሆነዋል። አይገርምም። እየመረጡ ማልቀስ ይሉሃል እንዲህ ነው። ሰው በዘሩ፤ በቋንቋና በሃይማኖቱ እይታ ብቻ ለሰልፍ ከቆመ ከቄራ ከብት በምንም አይሻልም። በጎንደር ለተፈጠረው ግድያና ዝርፊያ ተጠያቂዎቹ በህግ መጠየቅ አለባቸው። ግን እኮ ምንም ያላረገ ወገኑን የገደለ ፍጡር ለገዛ ቤተሰቡ ደህንነትም አያሰጋም? ውጊያና ፍትጊያ ከፈለጉ ይኸው ወያኔ በ 12 ክፍለ ጦር ራሱን አደራጅቶ ግጠሙኝ እያለ አይደለም። ሂድና ተፋለም እዚያ። የወስላታ ጋጋታ ከተማን ያጨናንቃል እንጂ ለሃገርም ለወገንም ደህንነት አይረባም። ሁሌ አካኪ ዘራፍ፤ ሁሌ ያዙኝ ልቀቁኝ፤ ሁሌ ፉከራና ቀረርቶ አይሰለችም? ህይወት እኮ የምትመዘንበት ሌላ ብዙ አይነት መንገድ አለ። I will bear witness: A Dairy of the Nazi years, 1933-1941 በተሰኘው መጽሃፉ ላይ Victor Klemperer እንዲህ ይለናል። ከምርጦቹ የአሪያን ዘሮች ያልሆኑት ከሞትም ቢተርፉ ናዚ ጀርመኒ በምታስዳድራችው ሃገሮች ላይ የሚቆጠሩት እንደ እቃ ነበር ይለናል። ግፈኞች ሲሰፍሩም ሲሰፈርባቸውም ጸጸትን አያውቁም። አብሮ መኖር በዓለም ዙሪያ ለእነርሱ ጥቅም እስካልሆነ ድረስ ዓለም ራሱ አብራ ብትቃጠል ደንታ የላቸውም። በተለይ ደግሞ በሃሰተኛና ያለ ቅጥ በተጋነነ የእምነት ጎዳና ውስጥ የገባ ማንም ሰው አይኑን ገልጦ የሌላውን ችግርና መከራ ለማየት አይቻለውም። ሁሌ በደላችን፤ ሃጢአታችን እያለ ይለፋል። ሰውን የሚበድለው ሰው ነው። ፈጣሪ አይደለም። የችግሩና የመከራው ሁሉ አዝናቢዎች እኛ ነን። በጎንደር የሆነውም ጢቢራቸው በተጣመመ የእምነት ዘይቤ በዞረባቸውና ሃገርን ለማፍረስ በተሰለፉ ቅጥረኞች የተፈጸመ በደል ነው። ነገሩን እንደማርገብ እያራገቡ ነዳጅ ማርከፍከፍም ተገቢ አይሆንም። እውነቱ ከሞቱት፤ ከተቃጠሉት ቤቶችና መስጊዶች ጋር አብሮ ተቃጥሏል። የምንሰማው ወሬ ሁሉ የተዛባ፤ ቅንጫቢና አጨብጫቢ፤ የበለጠ እንድንዳማ ሆን ተብሎ የተለጠፈውንና የተጻፈውን ነው። እውነት በሃበሻ ምድር እንደ ትንኝ እድሜዋ አጭር ነው። ላፍታ ታይታ የምትጠፋ! ከመጠፋፋታችን በፊት ጊዜ እያለ እናስተውል። በቃኝ!ReplyLeave a Reply Cancel replyYour email address will not be published. Δ Previous Storyበደቡብ ኢትዮጵያ ኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ታልታሌ ወረዳ ቡሌደንቢ ቀበሌ ሰዎች በበሬ ፈንታ ቀንበር ሞፈር ላይ አስረው በመጎተት ሲያርሱ – DW Next Storyአዎ! የዛሬው ወለጋ ኦሮሞ ኢትዮጵያን ከመውረሩ በፊት የጥንት ስሙ ቢዛሞ ይባል ነበር! – አቻምየለህ ታምሩ Latest from Blog ደራሲና ገጣሚ፡- አበረ አዳሙ በአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ግጥም ደራሲና ገጣሚ፡- አበረ አዳሙ በአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ግጥም ጎጃም አቸፈር አገዛዙን በጣም አስደንግጧል | ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ የጦር አውሮፕላኖች በሽሬ ሰማይ ህወሃት ሌላ ጦርነት አወጀ ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ የጦር አውሮፕላኖች በሽሬ ሰማይ ህወሃት ሌላ ጦርነት አወጀ አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን የጀኔራሎች ግምገማ ሾልኮ ወጣ ” ከአቅማችን በላይ ሆኗል” የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዛቸው ጠፋ የጀኔራሎች ግምገማ ሾልኮ ወጣ ” ከአቅማችን በላይ ሆኗል” የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዛቸው ጠፋ
ትግሬዎች፤ አህመዲን ጀበል፤ጁዋር መሃመድ፤ኡስታዝ አቡበከር ሎቶሪ ወጣላችሁ ሰውን ስላም አትንሱት ብዙ ቤተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል ተከባብረን እንኑር አታቀጣጥሉት እናንተም የሰራችሁት ማስረጃዉ አለን።Reply
እብዶች የራሳቸውን ቤት አቃጥለው ድረሱልን ይላሉ ወይም ዘለው እሳቱ ውስጥ በመግባት አብረው ይነዳሉ። ጎበዝ አብደናል። አሁን ሰው በሃይማኖት ሳቢያ በዚህ ዘመን ይጋጫል? ይህ የሚያሳየው እየቆየን ኋላቀር መሆናችን ነው። የምታመልከው አንድ አምላክ የምትሰበሰብበት ሥፍራ የተለዬ መሆኑ ለብቻው ሰውን እስከ መገዳደል ያደርሳል? ግን ይህ ሁሉ ሸር ሃገርን ለማፍረስ ከታቀደው ሴራ ጋር አብሮ ይሄዳል። ለፈጣሪ ማንም ከማንም የበለጠ ቀናኢ ሊሆን አይችልም። የእስልምና እምነት ቤቶች እየነደድ የእኔ አትንኩ ማለትም አይቻልም። ተያይዞ መጥፋትና መንደድ እንጂ። ሲጀመር ሃይማኖት የሰዎች የማሰሪያ ገመድ ነው። በአስተሳሰብ ያስራል፤ ሰውን ያራርቃል፤ ያቀረበውን ያቀርባል የሚያሳድደውን ያሳድዳል፤ የእኔ እምነት ከአንተ ይሻላል በማለት ይለፋል። ይህ ሁሉ መለፋደድ ነው። የማንም ሃይማኖት፤ ወይም እምነት ከማንም አይበልጥም። እንዴት ባለ ምድር ነው ሰው ለቀብር ወጥቶ እንደ እንስሳ ተራርዶ ለመኖር ቃል የሚግባባው። የዚህ ሁሉ አትራፊ ሟችም ቋሚም አይደለም። የሃገሪቱን እንደ ጧፍ መንደድ የሚሹ የውጭና የውስጥ ሃይሎች እንጂ። ትላንት እልፍ ሰዎች በወለጋ፤ በአርሲ፤ በሃርርና በልዪ ልዪ ሥፍራ ሲታረድና ሲፈናቀሉ ሰላማዊ ሰልፍ ያልወጣው ሃበሻ አሁን ጎንደር ላይ በተጫረው እሳት ሳቢያ የራሳችውንም ለመጫር እንዲመቻቸው ተሰላፊ ሆነዋል። አይገርምም። እየመረጡ ማልቀስ ይሉሃል እንዲህ ነው። ሰው በዘሩ፤ በቋንቋና በሃይማኖቱ እይታ ብቻ ለሰልፍ ከቆመ ከቄራ ከብት በምንም አይሻልም። በጎንደር ለተፈጠረው ግድያና ዝርፊያ ተጠያቂዎቹ በህግ መጠየቅ አለባቸው። ግን እኮ ምንም ያላረገ ወገኑን የገደለ ፍጡር ለገዛ ቤተሰቡ ደህንነትም አያሰጋም? ውጊያና ፍትጊያ ከፈለጉ ይኸው ወያኔ በ 12 ክፍለ ጦር ራሱን አደራጅቶ ግጠሙኝ እያለ አይደለም። ሂድና ተፋለም እዚያ። የወስላታ ጋጋታ ከተማን ያጨናንቃል እንጂ ለሃገርም ለወገንም ደህንነት አይረባም። ሁሌ አካኪ ዘራፍ፤ ሁሌ ያዙኝ ልቀቁኝ፤ ሁሌ ፉከራና ቀረርቶ አይሰለችም? ህይወት እኮ የምትመዘንበት ሌላ ብዙ አይነት መንገድ አለ። I will bear witness: A Dairy of the Nazi years, 1933-1941 በተሰኘው መጽሃፉ ላይ Victor Klemperer እንዲህ ይለናል። ከምርጦቹ የአሪያን ዘሮች ያልሆኑት ከሞትም ቢተርፉ ናዚ ጀርመኒ በምታስዳድራችው ሃገሮች ላይ የሚቆጠሩት እንደ እቃ ነበር ይለናል። ግፈኞች ሲሰፍሩም ሲሰፈርባቸውም ጸጸትን አያውቁም። አብሮ መኖር በዓለም ዙሪያ ለእነርሱ ጥቅም እስካልሆነ ድረስ ዓለም ራሱ አብራ ብትቃጠል ደንታ የላቸውም። በተለይ ደግሞ በሃሰተኛና ያለ ቅጥ በተጋነነ የእምነት ጎዳና ውስጥ የገባ ማንም ሰው አይኑን ገልጦ የሌላውን ችግርና መከራ ለማየት አይቻለውም። ሁሌ በደላችን፤ ሃጢአታችን እያለ ይለፋል። ሰውን የሚበድለው ሰው ነው። ፈጣሪ አይደለም። የችግሩና የመከራው ሁሉ አዝናቢዎች እኛ ነን። በጎንደር የሆነውም ጢቢራቸው በተጣመመ የእምነት ዘይቤ በዞረባቸውና ሃገርን ለማፍረስ በተሰለፉ ቅጥረኞች የተፈጸመ በደል ነው። ነገሩን እንደማርገብ እያራገቡ ነዳጅ ማርከፍከፍም ተገቢ አይሆንም። እውነቱ ከሞቱት፤ ከተቃጠሉት ቤቶችና መስጊዶች ጋር አብሮ ተቃጥሏል። የምንሰማው ወሬ ሁሉ የተዛባ፤ ቅንጫቢና አጨብጫቢ፤ የበለጠ እንድንዳማ ሆን ተብሎ የተለጠፈውንና የተጻፈውን ነው። እውነት በሃበሻ ምድር እንደ ትንኝ እድሜዋ አጭር ነው። ላፍታ ታይታ የምትጠፋ! ከመጠፋፋታችን በፊት ጊዜ እያለ እናስተውል። በቃኝ!Reply
ደራሲና ገጣሚ፡- አበረ አዳሙ በአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ግጥም ደራሲና ገጣሚ፡- አበረ አዳሙ በአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ግጥም
ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ የጦር አውሮፕላኖች በሽሬ ሰማይ ህወሃት ሌላ ጦርነት አወጀ ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ የጦር አውሮፕላኖች በሽሬ ሰማይ ህወሃት ሌላ ጦርነት አወጀ
አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
የጀኔራሎች ግምገማ ሾልኮ ወጣ ” ከአቅማችን በላይ ሆኗል” የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዛቸው ጠፋ የጀኔራሎች ግምገማ ሾልኮ ወጣ ” ከአቅማችን በላይ ሆኗል” የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዛቸው ጠፋ