February 13, 2013
3 mins read

የአርቲስት ታምራት ሞላ የቀብር ሥነ- ሥርዓት ተፈጸመ

02


(ዘ-ሐበሻ) የአርቲስት ታምራት ሞላ የቀብር ስነ- ሥርዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ ተፈጸመ። በርከት ያሉ አድናቂዎቹና ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት በተፈጸመው የቀብር ስነስ-ር ዓቱ ላይ የአርቲስቱ የሕይወት ታሪክ ተነቧል። ከሕይወት ታሪኩ መረዳት እንደተቻለ አርቲስት ታምራት ሞላ በ19 36 ዓ.ም ከአባቱ ከፊት አውራሪ ሞላ ዘለለውና ከእናቱ ከወይዘሮ አበራሽ የኔነህ ፥ በጎንደር ከተማ ተወለደ። ባለ ትዳር እና የ3 ወንድ እና የ2 ሴት ልጆች አባት የነበረው ይኸው አርቲስት በ19 53 ዓ.ም ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ከአጎቱ ጋር በመምጣት በክቡር ዘበኛ የልጅ ወታደር በመሆን የሙዚቃውን አለም አሃዱ ብሎ እንደጀመረ የሚያስረዳው የሕይወት ታሪኩ ከአራት አመት በፊት ባጋጠመው ህመም ሳቢያ በአሜሪካ እና በታይላንድ ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ በ69 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።
በ19 55 ዓ.ም አብዛኛውን የሙዚቃ ህይወቱን ያሳለፈበትን የምድር ጦር ሰራዊትን የተቀላቀለው አርቲስት ታምራት ፥ ሃገራዊ ፣ ማህበራዊ እና ፍቅርን መሰረት ያደረጉ ሙዚቃዎችን ከመጫወቱ ባለፈ ድራማ እና ቲያትርን ምክንያት አድርጎ መድረክ ላይ መቆም መቻሉን ከተነበበው የሕይወት ታሪኩ መረዳት የተቻለ ሲሆን በተለይም ትግላችን በሚል ቲያትር በመሪ ተዋናይነት ለመጫወቱም ባለፈ ፥ የበርካታ ዜማዎች ድርሰትን ቀምሮ ለህዝብ አቅርቧል።
በሃገር ፍቅር ቲያትር ቤት ለረጅም ጊዜያት በድምጻዊነት ያገለገለው አርቲስት ታምራት ፥ ከ50 አመታት በላይ ባስቆጠረው የሙዚቃ ህይወቱ ከአድማጭ ጆሮ የማይጠፉና የማይረሱ ሙዚቃዎችን ተጫውቷል።
አርቲስት ታምራት ሞላ ለረዥም ጊዜ በደም ካንሰር ሲሰቃይ እንደነበርና ከዚህም ህመም በጸበል መፈወሱ ይታወሳል። ድምጻዊው ሙዚቃ አቁሞ መዝሙር ለመዘመር ሃሳብ እንደነበረውም በአንድ ወቅት መናገሩ አይዘነጋም።

habtamu
Previous Story

Hiber Radio: ፒያሳ የሚገኘው እሳት አደጋ እሳቱ ከጠፋ በኋላ መምጣቱ በነዋሪዎችና በአካባቢው ፖሊሶች ላይ ቅሬታ ፈጠረ

Next Story

“በኢሕአዴግ መንግስት የሕግ የበላይነት ጭላንጭል በሐገራችን እየተዳፈነ ነው” – (ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop