የ”ቅዱስ” አባታችን ፣ የኢትዮጵያ ወይስ የትግራይ ፓትርያርክ ለሌላው ሕዝብ ሌላ የሚቾህለት ፓትርያርክ ሳያስፈልግ አልቀረም

ሰሞኑን ቤኒሻንጉል ላይ በትግራይ ተወላጆች ላይ ተፈጸመ የተባለው ጥቃት የሰውን ልጆች ልቦና ሁሉ ያደማል፡፡ በዚህ ልዩነት የለም፡፡ በየትኛውም መልኩ ቢሆን ወንጀል መወገዝ አለበት፡፡
ጥያቄው ግን ፣ የሁሉ አባት ተደርገው የሚታሰቡት አባት (የፓትርያርኩ) መርጦ ለቅሶ ነው፡፡
ፓትርያርክ ማቲያስ፣ የትግራይ ሰዎች ተጎዱ ሲባል ለመናገር ፈጣን ናቸው፡፡ ሚድያ ፈልገው አያጡም ፡፡ ሲፈልጉ በፈረንጅ በኩል፣ ሲፈልጉ በተወገዘው ቲኤሜች በኩል ለመናገር ፈጣን ናቸው፡፡
ወንጀልን ማውገዝ መልካም ነው፡፡ ግ ን ሀገር የሚመራ የሃይማኖት አባት መርጦ ሲያለቅስ ያሣስባል፡፡
አባ ማቲያስ ፣ አፋር ላይ ያ ሁሉ ሰው ሲያልቅ ምነው ድምጻቸው አልተሰማ? አነ ጭና ተክለሃይማኖት የመሰሉ ቦታዎች ላይ ያ ሁሉ ሰው ዘር እየተመረጠ ሲያልቅ ፓትርያርኩ ምነው አፋቸው ተለጎመ፡፡ እነ ማይካድራ ላይ ፣ ወለጋ ላይ ፣ ዘር እየተመረጠ ደም ሲፈስ ምነው አፋቸው አልተላቀቀ፡፡ወይስ ለሌላው ሕዝብ ፕትርክናቸው አይመለከተውም?
እንደ አባት ፣ ለሰው ዘር ሁሉ ይልቁንም ደግሞ ለተሾሙበት ኢትዮጵያ ሁሉ እኩል ማልቀስ ሲገባዎ፣ አባታችን ድምጻቸውን የሚያሰሙት ለአንድ ብሔር ብቻ ነው፡፡
አባታችን የትግራይ ፓትርያርክ ወይስ የኢትዮጵያ ፓትርያርክ?


ከፎቶው ላይ ካቦርታ ለብሰው ፊት ለፊት ገጭ ብለው የምታዩአቸው የድሮው አባ ኃይለማርያም የአሁኑ ፓትርያርክ አባ ማቲያስ ናቸው። ፎቶውን የተነሱት ለወታደራዊ መንግስት ደርግ ለፖለቲካ ሥራ ወደ ጎንደር ስሜንኛ በሄዱበት ወቅት ነው። አባ ማቲያስ በሁለት የተለያዩ መንግስታት ሁለት እየቅል የሆኑ ፓርቲወችን (ኢሰፓና ኢህአዴግ) ፖለቲካ ሲያስፈጽሙ የኖሩ ጀግና የሃይማኖት መሪ እንደሆኑ መረዳት ችለናል። ስንቱ አባት ገዳም ተቀምጦ እኚህን አንዴ አሜሪካ ሌላ ጊዜ አውሮፓ፣ ሲፈልጉ ኢሰፓ ደግሞ ሌላ ጊዜ ህወሓት የሚሆኑት ፓትርያርክ ከሰሞኑ ደግሞ አይን ያወጣ ወገንተኝነት ያለው መልክት አስተላልፈዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ተማሪዎች እና መምህራን በተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶች ላይ ሲሳተፉ ውለዋል

ነጋሪት – ዜና ጎንደር

8 Comments

  1. With all his human (Tigrayan) weakness, Abune Matiyas is our Patriarch. He is still human and could not escape the cultural underpinnings of being a Tigrayan. For the great majority, clan comes above religion, moral, ethics etc. It is an integral part of their identity.
    Lijin siwedu kene minu indemibalew wendimochahinin kene amelachew linawqina liniqebelachew ye ghid new. Igziabher iskiTerachew abatachin abatachin nachew. Lesachewim iyeTselayin kemeguaz wuchi mircha yellem. Ye derghina yeweyannen newrur lindeghim anichilm.

  2. እውነትም አሳፋሪና ጨካኝ ተግባር ተፈጽሟል። ነገር ግን በተደጋጋሚ ጊዚያት ዘግናኝ ድርጊት ሲፈጸም የት ነበሩ? ለመናገር እድል አላገኘሁም ይሉናል ለምን ታዲያ አሁን እድሉን ካገኙ ሁሉም ቦታ ስለተፈጸመው አልነገረንም ?
    እኔ እንደሚመስለኝ የወያኔ ደጋፊዎች የተቀናጀ ዘመቻ ላይ ናቸው። ዘመቻዎቹ ከዶር ቴዎድሮስ እስከ ፓትሪያርኩ የተሳሰረ ነው። ይህንንም እንዲፈጽሙ ደብረጽዮን ቡራኬውን ተሰጥተዋል እና የዛ ዘመቻ አካል ነው።

  3. Alemu እንጽልይላቸው ያልከው ከምርህ ባይሆንም እዚህ ጉዳይ ላይ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቻለሁ። ለመሪዎች ጸልዩ ጌታ ነው በዛ ያስቀመጣቸው የሚል ነገር አለ። ይህ የሰው ልጅ ከአምላኩ በቀጥታ በሚገናኝበት ጊዜ ነበር። ይህን ተከትዬ ለመለስ ዜናዊ፣ለሂትለር፣ለመንግስቱ ሀይለማርያም፣ለሀይለማርያምና ለአዲሱ መሪያችን ብጸልይ የህዝቡን መከራ አብዛው ብሎ ከመጸለይ ይቆጠራል። ቄስ ግርማን እንድንጠይቅ ዋናው ካድሬና ዘረኛ ሁነዋል

  4. Mr Deacon Daniel Kibret is a guy famed for his fictitious stories , throwing famous plagiarized quotes at his gullible audience who think he is a true follower and trustworthy servant of Orthodox church, and eventually all what he did and is still doing is for his personal advantage by throwing  dust in our  eyes as his most recent acts exhibited his genuine personality-unmasked true self. In the history of our church, we don’t have a pastor regarded as a good leader and who promotes genocide and seed hostility among neighboring tribes who share the same religion and take part in the same ecclesiastical sacred moment.

    He is simply a demon in the flesh and famous pulpit artist who hide his true self-portraits in his sermons and religious articles. What he preaches, and his deeds do, contradict to each other.
    Most Ethiopian Orthodox church pastors (preachers), and the rest of the clergy, dedicated much more time preaching about prayers, alms giving and fasting to their laity, but the current interethnic conflict and brutality demonstrated among the laity of Ethiopia orthodox church and other churches provoked a sentiment that all those sermons and clergy men failed to cultivate morality and personality of good Samaritan among Christians.

    Even many of our preachers like Daniel Kibert and so called Mahibrekidusan were very much obsessed with the number of their fans and followers while defaming good servants of church , some of whom left the church and joined other Christian denominations, but do invested little to no time and knowledge to unite their followers who belong to one & the same Orthodox church other than diving them among preachers. Most preachers spent their time speaking about themselves , their favorite football team, political party and royal king that they want to see him assume power -only building their image and hit the jackpot-achieve fame.
    “But as for you, you have turned aside from the way; you have caused many to stumble by the instruction; you have corrupted the covenant of Levi,” says the Lord of hosts, spoken about clergymen like Deacon Daniel by Malachi 2:8
    People like him caused many to stumble and go astray in their hearts and past true religious life by instilling hate and revengeful sentiment against each other
    Why is he not willing to speak up for Christians dying in Tigray ? Why not for all Tegaru irrespective of their religion ???

    The Samaritans were a group of people residing in Samaria, who did not have good relations with the Jews.
    Luke 10:25-37 In the context of religious teachings as it is mentioned the parable of Good Samaritan , we need to help anyone in danger and undergoing sufferings regardless of his ethnicity, religion and social category.

    His Holiness was defensive and had already advocated for all Ethiopians regardless of their ethnicity and religion , and many of you are not happy because you don’t want to hear His Holiness exposing the war crime committed against Tegaru, but the naked truth is that you want every church leader to condemn only and only TPLF.
    If you were looking for a cue of what to pick for a pretentious and crooked man among clergymen , look no further than Mr Deacon Daniel Kibret.
    Daniel Kibret and all other preachers should preach about peace, love, and advocate for all people subjected to genocide, displacement, hunger, and all sorts of sufferings. Please show us in your deed by speaking about Tegaru and Oromos ,if you are a true preacher and even if you consider yourself as a laity of Orthodox church.
    But he said, “Blessed rather are those who hear the word of God and keep it!”( Luke 11:28 )  So whoever knows the right thing to do and fails to do it, for him it is sin.( James 4:17 )Every clergy is a laity and must be faithful to God and act accordingly !!!!

    Man is least himself when he talks in his own person. Give him a mask, and he will tell you the truth. – Oscar Wilde

    A mask could be a beer, money under the table(bribe), also could be a historical moment like we have to day that every brutal and crooked man shamelessly wage genocide on our people just because the time has come to reveal his true self, and he finds himself in an era in which many people of the same behavior co-exist and acknowledge genocide as a norm and his criminal act received an approval from the majority.

    Stop Killing Tegaru, Amhara ? Oromos, Agew, Kimant , Gumuz, and all other tribes for their ethnicity and personal and political views . Stop Burning, and torturing humanity!!Abiy and his cliques(Fanos, Amhara elites including Dn Kibret -fake pastor – should step down and face justice!!

    • The patriarch` s claims of genocide against the Tigraians is proof that fascism as an ideology has gripped the Tigraian elites including the clergy. The TPLF cadres who pose as clergy are embedded in the Ethiopian Orthodox Church and are desecrating it. Therefore, it is important to embark on the de-fascistization of Tigray (ridding Tigray of fascism) for the sake of the Tigraians themselves.

  5. ለገባው አባትም ቅድስም የለም። ዝም ብሎ አሸንክታብ ማብዛት ነው። ለላይኛው ጌታ አድሬአለሁ የሚሉ ዘር እየመረጡ ሲያለቅሱ ከማየት የበለጠ ወስላታነት የለም። ሆዳቸው በሳንጃ እየተቀደደ እዚህ ምድር ላይ አንቺ ልጅ አትወልጂም እየተባሉ፤ የወደድከውን ባንዲራ ልበሰው ተብለው እየተጎተቱ የተገደሉ፤ በገደል ተገፍትረው የተጣሉ፤ በወያኔና በኦነግ ሸኔ ሽንክ ሥራ በወሎ፤ በጎንደር፤ በአፋር በሽዋና የኦሮሞ ክልል እየተባሉ በሚጠሩት ስፍራዎች ለደረሰው ሰቆቃ ምንም ድምጽ ያላሰሙ አሁን እሳት እንደነካው የባህር ማሽላ ቢንጫጩ ያው የዘመኑን የዘር ሰልፍ ካምፕ ለመምሰል እንጂ ሌላ መላ የለውም።
    ሲጀመር የሃይማኖት መሪ የሆነ ማንም ሰው በዘሩ ተሰላፊ ከሆነ እምነቱ ባዶ ነው። ግን ሃይማኖት የገንዘብ ማግኛ ብልሃት በሆነበት የአስረሽ ምቺው ጊዜ ማን የሚታመን አለና ነው? በወያኔ ጊዜ በአንድ እጃቸው መስቀል፤ በሌላው ሽጉጥ የታጠቁት የሙታን ሥራ አስፈጻሚዎች ዛሬም ሥራ አልፈቱም። ለእውነት የቆመ ሰው ለሁሉም በሁሉም የሰው ጉዳት ያዝናል እንጂ ዘርና ቋንቋውን ወይም ሃይማኖቱን እየመረጠ አልቅሶ ሌላውን አያስቅም ወይም አያስለቅስም። በትግራይ ልጆች ላይ በተፈጸመው በደል አይሰማኝም ይበላቸው የእጃቸው ነው የሚሉም ከሰው ተራ የወጡ ነገ የእነርሱ ወረፋ እንደሚሆን የዘነጉ እብዶች ናቸው። ሰውን በሰውኛ መመዘኛ መመዘን እስካልተቻለ ድረስ መርጠን ማዘናችን ይቀጥላል።
    ዛሬ በዪክሬን ላይ ያለው የወሬ ጋጋታ የሚያሳዬን ነጩ አለምም ሲያለቅስና ኡኡታ ሲያሰማ እየመረጠ መሆኑን ነው። የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም እንዲሉ አሜሪካንና አውሮፓን ተስፋ በማድረግ ራሽያን አፍንጫህን ላስ እኔ የኔቶ አባል እሆናለሁ በማለት የደነፉት ዪክሬኖች አሁን ማን ያድናቸው። ያለና አዲስ የተሰራ የጦር መሳሪያ መሞከሪያ ሲሆኑ እሳት ከማቀበል ሌላ ምዕራባዊያን ያደረጉላቸው የለም። ሃገሪቱ ወደ ኋላ 50 ዓመት እንድትጎተት ያደረገው ይህ ጥቃት ገለባና እሳትን አገናኝቶ የምዕራቡ ወሬ አቀባዪች መነገጃ ሆኗል። ይህ ጉዳይ በጥቁር መሬት ላይ የተፈጸመ በደል ቢሆን ኑሮ ነገርየው ከወሬም አይበቃ። ሰው ዛሬ ከምናየውና በፊትም ካለፈው የሃገሮች ታሪክ እንዴት መማር ይሳነዋል።
    አሜሪካ ሃገር በማፍረስ እንጂ ሃገር በመገንባት አትታወቅም። ለዚያ ነው ከወያኔ ጎን ተሰልፋ ነገሩን ሁሉ የምታተራምሰው። ጆኖሳይድ ያደረገው ወያኔ ሆኖ እያለ የትግራይ ህዝብ ጀኖሳይድ ደረሰበት ይሉናል። ለዚህም ነው የጳጳሱም ጭኸት ልክ እንደ ዓለም ጤናው ዳሬክተር በዘርና በቋንቋ ላይ ብቻ ያተኮረ የሆነው። የሙታን ፓለቲካ እንደዛ ነው። ምንም ፊደል ቢቆጥሩ ሁሌም እይታቸው አፍንጫቸው ጫፍ ላይ ነው።
    ባጭሩ በትግራይ ተወላጆች ላይ የደረሰውና የሚደርሰውን ግፍ ማንም ቆሞ ሊያይ አይገባም። ነገ በእኔም ላይ ይደርሳል ወይም ተመሳሳይ ነገር ደርሶብኛል የሚል ሰው ለእውነትና ለፍትህ ሊቆም ይገባል። ግን እኮ መቼ ነው ሃበሻው በጎሳውና በዘሩ በድንበሩና በሃይማኖቱ ብቻ እየታከከ በሃሳብም ሆነ በሰላ መሳሪያ ሲፈናክት የሚኖረው? መቼ ነው እናቶች፤ እህቶች፤ ሽማግሌ አዛውንቶች እፎይ የሚሉት? ያ ቀን ይመጣ ይሆን? ወይስ ዝም ብለን ስንናቆር ጀመር ወጥታ ትጠልቃለች? በቃኝ!

  6. አሁንስ ግራ ገባን እኮ፥፥ከአማርኛ ና ኤንግሊዘኛ ባለፈ ሌላ ቋንቋ ትናገራለህ አቦ ተስፋ፥ሊረዳህ ከቻለ በሌላ ቋንቋ እናሥረዳሃለን፥በብዙ ልሣኖች የሚግባቡ ሊቃውንት አሉን፥ሃሳብ አይግባህ፥፥የጠረጠርነው ነገር ቢኖር ሾርት ሜሞሪው አዕምሮህን ካጠቃ ስለከራረመ ያለጥርጥር ወደ ክሮኒክነት (ስረሰዳጅነት፡ዘላቂነት)ተቀይሮ ስንኳንስ ቅዱሥ አባታችን በሻሸመኔና በሌሎችም አካባቢዎች በግፍ ስለ ተገደሉ ሕዝበ፥ክርስትያኖች ኢትዮጵያውያን ሁሉ ያለቀሱትና የተናገሩት ትናንት የበላኸው ምግብ ና ጉሮሮህን ያቧጠጠው ካቲካላ ይታወሥህ አልመሰለኝም፥፥ሁላችሁም የአማራ ሊቃውንት ጨርሶ ይማራቹህ፡፥ህመማቹህ ለህዝባቹህ እና ለመላው ሀበሻ ሁሉ ተረፈው እኮ ኩፉኛም ጎዳው፥፥ዘር ፥ጎሣ ሃይማኖት መርጦ ማልቀሥ ከናንተ ነው ያየነው፥፥የክፋትና የጠባብነት፥የዱለታ(ሴረኝነት )በኩር እናንተ ናቹ፥፥፥፥ሲጀመር ቅዱሥ አባታችን ጎሣ ለይተው ወይም ሥም ጠርተው በዚህ ስም የሚጠሩ ና የታጠቁ የአንድ ወይም የሁለት ብሔር አባላት በቅንጅትም ሆነ በተናጠል በትግራይ ሕዝብ ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ፈፀሙ አላሉም፥፥አንዱን ከሌላው ብሔር ነጥለው ለትግራይ ሕዝብ ዕልቂት ተጠያቂ በፍፁም(በጭራሽ)አላደረጉም፥፥ምን ያለበትሥ ዝላይ አይችልም ነው የሚሉት ባለ ተረቶቹ (የተረት አባቶቹ)፥፥
    ጆኖሳይድ ያደረገው ወያኔ ሆኖ እያለ የትግራይ ህዝብ ጀኖሳይድ ደረሰበት ይሉናል ትላለህ ጥቂት ሳትቆይ በዚሁ ፅሑፍ መልሰህ ባጭሩ በትግራይ ተወላጆች ላይ የደረሰውና የሚደርሰውን ግፍ ማንም ቆሞ ሊያይ አይገባም። ነገ በእኔም ላይ ይደርሳል ወይም ተመሳሳይ ነገር ደርሶብኛል የሚል ሰው ለእውነትና ለፍትሕ ሊቆም ይገባል በማለት አንዴ የክህደት ሌላ ጊዜ ደግሞ አዛኝ ቅቤ አንጓች ሰብዕናህን ያለ ፍላጎትሕ ከጥርስ ተፈልቅቆ አንደወጣ ሥጋ ወጥቶ ይታይብሃል፥፥ራስሕንና አንተ ስፖንሰር ያደረግሃቸው ነፍሰ በላዎች ፋኖዎችን ከተጠያቂነት ነፃ ለማውጣት ስትሉ ጀኖሳይድ በትግራይ እንዳልልፈፀመ ላማስመሰልና ለመካድ ያላደረጋችሁት የለም፥፥በብዙና በተደጋጋሚ ጊዜያት እየተስተዋለ የመጣና ሁሉም የማይዘነጋው ባህርያቹ ቢኖር በረጃጅም ፅሑፎቻቹ የተለያዩ ሀሳብ ያላቸውን እውነት የሚመስሉ ታሪኮችን አንባብያንን በማጎራረስና ከርዕስ ሀሳቡ በማሥወጣት ተቀባይነትን ማሥፋት ነው፥፥ተያያዥነት የሌላቸውን ሃሳቦች በመንዛት የአድማጭም ሆነ የአንባብያንን ልብ ለመማረክ በሚል ዓላማ የተመሠረተ አካሄድን በመጠቀም የሚታዎቁ የመድረክ አርቲስቶች ሰባክያኑም(ዲያ ክሥረት) ሞልተዋችሗል፥፥እንደ ኢሳትና ሌሎችም ጸረ ትግራይ አክቲቪስቶች በትግራይ ሕዝብ ላይ የጅምላ ጭፍጨፋን ሲቀሰቅሱና ሲያውጁ የኮነነና የክፋት መርዛቸውን ያስጣለ አልነበረም አልታየምም ይልቁንም በሃይማኖታዊ በዓላት ላይ ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በከፍታ ላይ እንደምትገኝ እና የትግራይን ሕዝብ ለማጥፋት በሚደረገው ኢሳት ና ሕግደፍ ሰራሹ ጦርነት ያሳዩት ምሳሌ አልባው አጋርነትና ህብረት ብዙዎቻቹህ ህግደፋውያኑን ያለ ሀፍረት ስታዳንቁና ስታሞጋግሷቸው ከማየት ባለፈ በትግራይ ሕዝብ ዕልቂት በመደሠት የአብሮነታቹ ማሳያ የሚሆን ካቲካላ ስትቋደሱና ስትጨፍሩ ያየንባቸው ቀናት አልተዘነጉም ፥፥የቅርብ ጊዜ ትውሥታችን ስለሆኑ አንድም እንደናንተ የሾርት ሜሞሪ ተጠቂዎች ሥላይደለን ነው ፥፥የተጋሩ የኦሮሞ፥ቅማንት አገው ጉምዝና እና ብሔር ተኮር የሆነ በማንኛውም ሕብረ ብሔር ላይ የሚደረግ የጅምላ ሆነ የተናጠል ግድያ እሥራት፥ ማሰቃየት፥ ዝርፊያ ይቁም ፥በዚህም ሰይጣናዊ ፥ኢሰብዊ ኢሃይማኖታዊ ተግባር የተሰማራ ሁሉ ለህግ ይቅረብ ሥርዓት ባለው መልኩ ህጋዊ ቅጣት ይቀጣ፥፥ሰላም ፤ድል ነፃነት ለንፁሓን ወገኖች ሁሉ ይድረስ፥፥አሜን፥፥

  7. ብጹእ አባታችን በ ፓራኮማንዶ ዩኒፎርም ማውጣት መልካም አይመስልም አቀማመጣቸውና ንቃታቸው ግን በዚህ ነገር ስልጠና የወሰዱ ይመስላል አዘውትረው ስለመታፈን የሚያወሩት ግን ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ቢሮዋቸውና መኝታ ወይም መዝናኛ ክፍላቸው ዉስጥ በቂ አየር ሊኖር ስለማይችል ጽ/ቤታቸው ደረጃውን የጠበቅ ቨንቲሌተር ቢያስገጥምላቸው መልካም ነው እላለሁ። ወታደራው ስልጠና የወሰዱ አባት ምቾቴ አልተሟላም ብለው የሚያዝኑ አይመስለኝም ችግር ካልሆነባቸው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share