አንተም ተው አንተም ተው

 semere.alemu@yahoo.com

ባለፈው በአበበ ገላው ቡድንና በኤርምያስ ለገሰ መካክል መወነጫጨፍ ተጀምሮ ወደ ክስ ማምራቱን ሰምተን እልኻቸው ሲበርድ ተስማምተው ለዚች አገር ዉል ያለው ስራ ይሰራሉ ብለን ብንጠብቅም ነገሩ ስር በስር እንደ ሰደድ እሳት ተቀጣጥሎ መዝገብ ተከፍቶ፤ እማኞች ተጠርተው በፈረንጅ ፍርድ ቤት ሊዳኙ ቀጠሮ መያዙን እያዘንን ሰማን። በስንቱ ሃገር የተቀጣጠለውን እሳት ያጠፋን ኢትዮጵያዉያን እሳቱ እኛው መሀል ገብቶ ሲፈጀን እያየሁ መቀመጥ ስላላስቻለኝ ቢሰሙኝ ብዬ ባድራሻቸው ሊደርስ ይችላል በሚል ግምት ወደ ድር ጥንጥን መልእክቴን ላክሁ።

በአንድ ወቅት ኤርምያስ ለገሰ የግምቦት 7 አባሎች፤ የዲሲ ግብረ ሀይልና ካምፓኒያቸው በስልክና በተለያየ የመገናኛ መስመሮች  ያስፈራሩኛል አሜሪካ የሰጠችኝን መብት ተጋፍተውኛል በማለት በሚሰራበት ሚዲያ ወገን እንዲያዉቅለት ከገለጸ በኋላ አበበ ገላው ኤርምያስ ለገሰን የዲሲ የህወአት ሰው፤ የበረከት ስምኦን ተወካይ በማለት የመልስ ምት ሰጠ። ነገሩን በመለጠጥም እንግሊዝኛ ያለ መቻሉንም ጠቆም አድርጎ አለፈ። ይህንን ታክኮ ደረጀ ሀብተወልድም ኤርምያስ ዶ/ር አብይን አላግባብ ተጋፋው በማለት በአንድ ዝግጅቱ ብቀላ በሚመስል መልኩ የአማራና የኦሮሞ ጠላት አድርጎ በቅንብር አቀረበው።

እንግዲህ የዚህ ነገር ክሩ ሲመዘዝ ለኢትዮጵያ ምንም ፋይዳ ላልሰራውና ለኢትዮጵያ እዳ ከሆነው የግምቦት 7 ድርጅት ጋር መያያዙን የኢትዮጵያ ፖሊቲካን ለተከታተለ እምብዛም ስውር አልነበረም።  አበበ ገላው፤አንዳርጋቸው ጽጌ፤ነአምን ዘለቀ፤ብርሃኑ ነጋና መሰሎቻቸው በኢሳት ቆይታቸው ለኤርምያስ ሰፊ ሽፋንና የአየር ሰአት ሲሰጡት ከበረከት ስሞን ጋር መስራቱን ሳያውቁ ቀርተው አልነበረም እንደውም የገረማቸው እንዲህ ያለ ወምበር ጥሎ መሰደዱን ነበር። በእርግጥ እንደ ኤርምያስ ያለ ከአንድ አርስት ወደ ሌላ አርእስት እራሱን እየወረወር ማብራሪያ የሚሰጥ ተንታኝና ጋዜጠኛ በእውቀትና በልምድ እራሱን የካበተና የአይን ምስክርነቱን የሚሰጥ እውር ድምብሩ የጠፋውን ኢሳትን ጥሎ ሌላ ሚዲያ መመስረቱ ድንጋጤ መፍጠሩ አይቀሬ ነበር።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የዘመኑ መንፈስ (በእውቀቱ ስዩም)

ኤርምያስ ከወያኔ ጋር ሰርቷል አንዳርጋቸውም ወያኔ ሲደናበር ጣቱን ይዞ ለአዲስ አበባ ህዝብ አስተዋዉቆታል፤ ዶ/ር ብርሃኑም መለሰ ዜናዊ አላመነውም እንጅ በህወአት አካባቢ ዉር ውር ሲል ነበር የዩኒቨርስቲ መምህራን ሲባረሩም መለስ ዜናዊን ለማስደሰት ገብቶ ሲሰራ ነበር። ኤርምያስን ከነ ግምቦት 7  የሚለየው እነ አንዳርጋቸው ጽጌ ህብረተሰቡን የሚከፋፍል ጽሁፍ እየጻፉ ልዩነትን መተዳደሪያቸው ሲያደርጉ ኤርምያስ ለገስ በተጻራሪው የህወአትን ክፉ ስራ ነቅሶ የህወአት አገዛዝን ብትንትኑ እንዲወጣ የረዳ ዜጋ ነበር። እንደሚባለውም የመጽሃፉን ሺያጭም ለኢሳት እንዳዋለው ከሌሎች ሲነገር ተደምጧል። ዛሬ ኤርምያስ ብቻውን የቆመ ይመስላል የግምቦት 7፤ የኢሳት፤ የዲሲ ግብረ ሀይል በጠንካራ የእውቀት መሰረት ላይ ቁመው ኤርምያስን ከመሞገት ይልቅ የነሱ አለቆች ወያኔና ሻቢያ ጋር እንዳልሰሩ ሁሉ እሱን ባለፈ ስራው ሊያሸማቅቁት ይሞክራሉ። በህወአት ቁጥር 1 እድሉ ያመለጣቸው ግምቦቶች በህወአት ቁጥር 2 ስልጣን የተሰጣቸው ተሰጥቷቸው ያላገኙት ሽራፊ ስልጣን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ። አበበ ገላው ኤርምያስ እንግሊዝኛ አይችልም ያለው በሱ ደረጃ ይህ አስተያየት ባይሰጥ መልካም ነበር እሱም በተለያየ ጊዜ እንግዶችን በእንግሊዝኛ ሲጠይቅ እንደ ሰሚ ያስተዋልነውን አስተውለናልና።እዚህ በፈረንጁ አለም ተወልደው የኛም ልጆች በተፈለገው ደረጃ የቋንቋው ክህሎት ላይ አልደረሱም እንግሊዝኛን አቀላጥፎ አለመናገርም የእውቀት መስፈርት ተደርጎ ባልተወሰደም ነበር።

እዚህ ላይ አበበ ገላው  ደጎስ ያለ መጽሃፍ ባይደርስም በተክታታይ የፖለቲካ ትንተናዎች ላይ እንደ ኤርምያስ ባናየውም  ለኢትዮጵያ ህዝብ የዋለው ዉለታ ግን እንዲህ በቀላሉ ሊረሳ አይገባም። አበበ ገላው ያንን የመርዝ ብልቃጥ በጌቶቹ መሀል ያለ አቅሙ ተኮፍሶ ቁጭ ባለበት በዛ ሃያል ድምጹ የኢትዮጵያ አምላክ ታክሎበት ላይመለስ የሸኘልን የክፉ ጊዜ ወንድማችን ነው። ይህ ጀግና ዉለታውን ኢትዮጵያ ትክፈለው ከማለት ሌላ ምን ይባላል? ይህ ገድሉ በታሪክ ሲጠቀስም ይኖራል።  ታዲያ የዚህን ግፈኛ ሰው (መለሰ ዘራዊን) አስመልክታ ሰላም በያን የምትባለው ምሁር ያበበ ገላውን ገድል ዉብ በሆነውና በተካነችበት የእንግሊዝኛ ቋንቋ እንዲህ አድርጋ አቅርባዋለች አንብቡት ሳይሆን አጥኑት እላለሁ።The Cause of Zenawi’s Death and Its Import | Ethiopian Uprising (wordpress.com) አቤም እንግሊዝኛን አድናቂ ከሆነ ይህን ጽሁፍ ያንብብ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ ህዝብ ትግል እንዴት ይመራ? የመነሻ ሃሳብ ሰነድ በመስከረም አበራ

አንድ ነገር ሳይጠቀስ ሊታለፍ የማይገባው ኤርምያስ ለገሰ ወከባ በበዛበት ጊዜ ይህን አጋጣሚ ሲጠብቅ የነበረው ቴዎድሮስ ጸጋዬ በተደጋጋሚ ጋብዞት በመሪ ጥያቄ እየነዳ በይሉኝታና የእሱ ያልሆነውን ሃሳብ እንዲናገር በመሰሪ አቀራረቡ መጥለፉንም ማስታወስ እንፈልጋለን ይህ ሃብታሙንም ይጨምራል። ሲጀመር ኢትዮጵያዊ የሆነ ሰዉ ወይም ተቋም በቴዎድሮስ ጸጋዬ ቦይ መፍሰስ አልነበረበትም። ኢትዮ 360ም ማንኛውንም ትንተና የሚዲያ ደረጃውን በጠበቀ  መልኩ ቢቀርብልን መልካም ነበር። የምንኖረው በምእራቡ አለም ሁኖ በእነሱ ደረጃና ከዛም በላይ መሆን እየተቻለ አንዳንድ ብሽሽቅ የመሰለ ነገር አቀራረብ ላይ ባይስተዋል መልካም ነበር። እዚህ ላይ የስራ ጫናችሁንም እንገነዘባለን በብዙ ሰራተኞች የሚሰራውን ስር በጥቂት ወገኖች ወደኛ ለማድረስ የምትደክሙትንም ጥረት ዘንግተን አይደለም በተቻለው ሁሉ ተቸገሩልን ማለታችን እንጅ።

ባጠቃላይ ዛሬ ኢትዮጵያ የነበረች ሃገር ሳትሆን ገና ልትመሰረት ዝግጅት የተጀመረባት ይመስላል። የሰሜን የባህር በራችን በትግሬዎች ለሻቢያ ተሰጥቷል፤ ስዩም መስፍንም ባድሜና ሽራሮ የትግሬ ግዛት አይደሉም ብሎ ለላይኛዉ ወገኖቹ አስረክቧል፤ የባንዳ ልጆች ብሄራዊ ክብረ በአል በደረሰ ቁጥር መሸማቀቁ ስለበዛባቸው ኢትዮጵያን አፍርሰው እፎይ ማለትን መርጠዋል። ፈረንጆችም በሃሳብ የተጎዱ ዜጎችን ተረት እየጋቱ አገራቸውና ወንድሞቻቸው ላይ እንዲዘምቱ አድርገዋል፤ ታሪካው ጠላቶቻችን አረቦችም የውስጥ ባንዳዎችን በመጠቅም አጥሩን በመነቅንቅ ላይ ናቸው። በዚህ ላይ መንግስት ለመኖሩም እርግጠኛ አይደለንም። ሹመት በዘር ነው አምባሳደሮቻችን ከኢትዮጵያ በተጻረረ መልኩ መግለጫ ሲስጡ (ሱሌማን ደደፎ፤ ሌንጮ ባቲ) አበጀህ ይባላሉ፤ መልካም ሰዎችና ህዝብ ተስፋ የጣለባቸው ወይ ይገደላሉ ወይ ወደ ጎን ይገፋሉ(ዶ/ር ስለሺ በቀለ፤ሙስጠፌ …) ዜጎች እንደ አዉሬ ሲገደሉ ለመንግስት ምኑም አይደለም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከቡሄ ትዝታዬ – አሁንገና ዓለማየሁ

ታዲያ አገር እንዲህ ምስቅልቅሏ በወጣበት ሰአት ለሀገራችን አብረው ቢሰሩ ብዙ ሊጠቅሙ የሚችሉ ኤርምያስ ለገሰና አበበ ገላው አስፈላጊ ባልሆነ እሰጥ አገባ ተጠምደው ጊዜያቸውን ማባከናቸው ልብን ያደማል። ኤርምያስም ሆነ አበበ ገላው መልካም ዜጎች ስለሆናችሁ ሁለታችሁም ሰይፋችሁን ወደ ሰገባው መልሳችሁ ለሃገራችሁ ትደክሙ ዘንድ በኢትዮጵያ ስም እንጠይቃለን። በተከፈተው ፋይል አገራችን ውስጥ አለም አቀፍ ወንጀልን የፈጸሙ፤ ዜጎችን ያረዱ፤ያቃጠሉ፤የሰቀሉ ወንጀለኞች በስልጣንና በጫካ በመኖራቸው የናንተን ፋይል ዘግታችሁ ወደዚህኛው ብታተኩሩ ምስጋናችን የበዛ ይሆናል።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር semere.alemu@yahoo.com

 

 

 

4 Comments

  1. In Ethiopia our people suffering every day, by genocide, hunger, and war imposed by the government in charge. our people are murdered day and night in hundred and our country is in the verge of collapse, however the hypocrite abebe is seeking a moral compensation ….……what a moral dose he has…. Last week one young Ethiopian burned alive by the government security personnel, how much compositions do we really owe him for letting this happen to him…ato abebe you are not more than those Ethiopians barbarically murdered and humiliated till death….. let it stop there and show us your integrity

  2. ግሩም ምክር በመሆኑ ቢቀበሉና ቢስማሙ መልካም ነው በፊርድ ቤት ጉዳዩ አልቆ አንደኛው አሸናፊ ሌላኛው ተሸናፊ በመባሉ የሚደሰቱ የጋራ ጠላቶቻችን ብቻ ናቸው።

  3. After everything is said and done, it is hard to compare Ginbot 7 with Ermias. For a year Andy was with TPLF and Berhanu was never with them. Tamirat Layne and Berhanu Nega went to the same high school and later on to AAU at 6 Kilo. Berhanu came home with a PhD in economics and led the economic association while regularly contributing to TOBIA magazine which was widely read. Beside his self-made father who is respected, Berhanu’s fame grew for what he was doing at home. His energy was boundless and he was lecturing at AAU and giving away the whole salary for charity. When he went into real state business, he paid the farmers for their land at market value. He was in fertilizer business too but that ended with TPLF kicking him out of it. At AAU, TPLF supporters were harassing him in lecture halls for every student to see. Nevertheless he was the most popular instructor with re-introducing some stuff which were but forgotten for years. At the national lottery hall, him and the late Prof Mesfin told the students what was their rights as students within the law. They were taken to prison and their case was lingering in courts while they were locked down. A few years later Prof Mesfin had an idea and that ended up with the formation of the Rainbow Coalition which created KINIJIT within six months and totally defeated TPLF in election. Berhanu was the hardest working guy in that unforgettable time, some times trying to make the two older parties agree deep into the night while they changed their negotiators at the table. Prof Mesfin would later say in his book that he had never seen a person working so hard than Berhanu.

    When KINIJIT chapter in USA betrayed the cause KINIJIT international led by Andargachew Tsige stayed loyal. They formed Ginbot 7 in memory of the election day in 2005 or 1997 in Ethiopian calendar. The main reason being there was no room for peaceful regular opposition party at home any more. Birtukan and Mesfin thought there was still some room but they were proven wrong and Birtukan went to jail for the second time. Andy became Ginbot 7’s general secretary and went to Eritrea to lead the yolk of it’s rebel army. Berhanu made a phone call to Prof Al Mariam and formed ESAT. Neamin led ESAT and made it the most dangerous media to TPLF. Journalists joined in and the late Mulegeta Lule became editor in chief and then Abebe Gelaw. When TPLF kidnapped Andy in Yemen, the likes of Efrem and Berhanu himself quit their jobs and went to the battle field. The anger over Andy’s kidnap was unprecedented and that scared the hell out of TPLF. Adhanom would try to show how forgiving it was on internet but that didn’t help either. The highly educated Muslim Diaspora that was moving Ginbot 7 behind the scenes called for public disobedience at home. That DIMITSACHIN YISEMA movement with it’s crossing the hands over the head was so disciplined and the beginning of the end for TPLF. When TPLF’s mistreatment of leaders of the movement was rerun at night on ETV, it was the uncut version and the damage was too much for repair. Ginbot 7 is no more but it will be remembered for being the first political organization led by well educated Ethiopians and a job well done.

    Neamin came back to the states and helped the cause of Ethiopia on Twitter. ShewaQena passed away in USA. Efrem went back home and is still making appearances on TV channels. Tadesse Biru won his case in UK and didn’t go to jail. Berhanu led EZEMA and is now minister of education. Andy is managing ESAT in Ethiopia.

  4. Lawyers or preachers who do not have substances talk endlessly. We didnt get any substances in your writing. That was not what Mesfin repeatedly told us about Berhanu, thanks to Berhanu EZEMA didnt get any seat in Parliament, G7 didnt gain any military victory while it was under the arms of Afeworki. Now Berhanu is unelected minister imposed on Ethiopians to serve Abyi and he is happy to do that even though he is rejected by Ethiopians, it. Is not possible to give political life to the people u mentioned above better to leave it to fade from people’s memory, the more you try to defend them the more punch u receive from every corner.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share