የብልጽግና ፓርቲ ኮንግረስ አብይ አህመድን ፕሬዝዳንትአድርጎ መረጠ

አንደኛ ጉባኤውን እያካሄደ የሚገኘው ብልጽግና ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ፕሬዝዳንት አቶ ደመቀ መኮንን እና አቶ አደም ፋራህን ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።
አንደኛ ጉባኤውን እያካሄደ የሚገኘው ብልጽግና የፓርቲውን ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ምርጫ እያካሄደ ነው።
በዚህም መሠረት
ለፕሬዝዳንትነት በሲዳማ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ የተጠቆሙት
ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ናቸው።
በጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ዑሞድ ኡጅሉ ለምክትል ፕሬዝዳንትነት የተጠቆሙት
አቶ ተመስገን ጥሩነህ ናቸው።
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አሻድሊ ሀሰን ለምክትል ፕሬዝዳንትነት የተጠቆሙት
አቶ አደም ፋራህ ናቸው።
በኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ለምክትል ፕሬዝዳንትነት የተጠቆሙት
አቶ ደመቀ መኮንን ናቸው።
በአሁኑ ሰአት ለጉባኤተኛው ድምጽ መስጫ ወረቀት እየተሰጠ ነው።
ውጤቱን ይዘን እንመለሳለን።
(ኢ.ፕ.ድ)

ሀሃሳብ እና አስተያትዎን ይስጡ

ተጨማሪ ያንብቡ:  Sport: "ራሴን የምመለከተው እንደ ቼልሲ አሰልጣኝ ብቻ አይደለም፤ ክለቡን ከልቤ እወደዋለሁ" ሞሪንሆ

1 Comment

  1. የደመቀ መኮንን ጸሀይ ጠለቅች ማለት ነው? ፖለቲካ ይሉኝታ አያውቅም አብይን ሸፍነህ ጥይት ልትቀበል የነበረውን ዛሬ ላይ የታሪክ ሰዎች ያስታዉሱት እንደሆን እንጅ አብይ አያስታዉሰውም። ከህዝባችሁ ጋር ብትቆሙ ዛሬ አብረን እንቆምላችሁ ነበር። አማራው ሲሳደድ ድምጻችሁን ብታሰሙ ብታስቆሙ ዛሬ ላይ ማእብሉን እንገድብላችሁ ነበር።አለምነው መኮንን፤ላቀ አያሌው፤ንጉሱ ጥላሁን፤አገኘሁ ተሻገር፤ገዱ አንዳርጋቸው፤ተመስገን ጥሩነህ…. እያለ በቀስታ ትደበዝዛላችሁ አብይ በናንት ቦታ የመረጠው ሌሎች የተተፉትን ነው ቅንጣቢዋን እየተከተሉ ይህን ያህል መዘናጋት ባላስፈለገ ነበር። አሳምነው ሲሞት አብይን ለማስደሰት ተራ በተራ ሰትገፋፉ አሳምነውን ለማውገዝ ዛሬ እዚህ ላይ ተደረሰ። የናንተስ አብቀቷል እናንተን ተክትለው እነበልተን እንሙት ከዚህ ቢማሩ መልካም ነበር አሁን ላይ ሁሉም አብቅቷል ከዚህ በላይ መዋረድም የለም።አሁን ላይ የነጋችሁ ጠ/ሚኒስቴር ሺመልስ አብዲሳ ላይ ወድቋል። እሱ ቁማሩን ሲሰራ እናንት ህዝባችሁ ላይ ታደቡ ነበር።፡አገኘሁ ተሻገር ይሰማል? እናንተ የምትተኩት የምትኮተኩቱት ከናንተ ይሻላል ብሎ መገመት ይክብዳል በረክት ስሞን ደኮድ ካላደረጋችሁ በሰሯችሁ አይነት መንቀሳቀሳችሁ አይቀርም??

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share