March 12, 2022
2 mins read

ፅንፈኝነት ሰላምንም ሆነ ፍትህን እውን ሊያደርግ አይችልም!!!

ሰሞኑን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ጉባ ወረዳ አይሲድ ቀበሌ እጅግ አሰቃቂ እና ከሰብአዊነት ያፈነገጠ ድርጊት ተፈፅሟል::

275339136 938006056909164 6678117389340028274 n 1በማህበራዊ ትስስር ገፆች በተንቀሳቃሽ ምስል ሲዘዋወር በቆየው እጅግ አሰቃቂ ድርጊት ንፁሃን ዜጎች በእሳት ተቃጥለው እንዲሞቱ ሲደረግ ታይቷል።
ይህ ድርጊት ከኢትዮጵያዊነት ባህል፣ እሴትና ከማንኛውም የሰብአዊነት እሳቤ ያፈነገጠና እጅግ አሰቃቂ ወንጀል ነው።
ይህ እኩይ ድርጊት መጠፋፋትን ያፈጥን ካልሆነ በቀር ሰላምንም ሆነ ፍትህን እዉን ሊያደርግ አይችልም:: በመሆኑም ሊኮነንና ሊወገዝ ይገባል::
መነሻቸውም ሆነ ማንነታቸዉ ምንም ይሁን ምን መንግስት ይህን አይነት ፍፁም ከሰብአዊነት የራቀና ጭካኔ የተሞላበትን ድርጊት የፈፀሙ አካላትን አጣርቶ ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሚታየውን ህገ ወጥነት ለመቆጣጠርና በንፁሃን ዜጎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመከላከልም ከክልሉና ከመላው የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን እየተሰራ ይገኛል።
የንፁሃን ዜጎችን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥሉ አካላትን መንግስት ከዚህ በኋላ አይታገስም።
ስለዚህ እነዚህ በወንጀል ስራ ላይ የተሰማሩና የዜጎችን ህይወት አደጋ ላይ የሚጥሉ አካላት ከወዲሁ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ መንግስት በጥብቅ ያሳስባል።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Amhara PP
abiy 1

Leave a Reply

Your email address will not be published.

275693327 539117197779540 6499245695507069949 n
Previous Story

በመርካቶ የ32 ቀበሌ ወጣቶች በብዛት ታሰሩ፣ ሰፈራቸውን ለቀው እየጠፉ ናቸው

275661939 508294267491561 5477151793991036021 n
Next Story

የብልጽግና ፓርቲ ኮንግረስ አብይ አህመድን ፕሬዝዳንትአድርጎ መረጠ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop