ከ400 በላይ የተባባሩት መንግስታት ድርጅት መኪናዎች ለጦርነት ሲውሉ የት ነበራችሁ?- ዜጠኛ ሄርሜላ አረጋዊ

የአሜሪካው ሲቢኤሲ ጋዜጠኛዋ ሄርሜላ አረጋዊ አሜሪካንን ትጠይቃለች
400 በላይ የተባባሩት መንግስታት ድርጅት መኪናዎች ለጦርነት ሲውሉ የት ነበራችሁ?
የትግራይ ታጣቂዎች ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በመግባት ሺዎችን ሲገድሉ ምን አላችሁ?
*******************************

መንግስት በኢትዮጵያ የውስጥ ጉደይ ላይ ገብተዋል፤ ከተፈቀደላቸው ዓላማና ተግባር ውጭ ሲንቀሳቀሱ ተገኝተዋል ያላቸውን 7 በዓለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ የሚሰሩ ግለሰቦችን በ72 ሰአታት ውስጥ የኢትዮጵያን ግዛት ለቀው እንዲወጡ ሲል ትናንት አዟል።

ይህንን ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ውሳኔውን ተቃውመው ጽፈዋል። ውሳኔውንም መንግስት እንዲቀለብስ ጠይቀዋል።

መስከረም 6 ቀን 2014 .ም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮ፤ ወደ ትግራይ የእርዳታ ምግብ ይዘው ከሄዱ 466 መኪናዎች ውስጥ የተመለሱት 38ቱ ብቻ ናቸው፤ ርዳታ ለማድረስ መኪና ያስፈልገናል ሲል አስታውቆ ነበር። በዚህ ወቅት ግን ዋና ጸሀፊው አንቶኒዮ ጉተሬዝ ሆኑ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ያሉት ነገር አልነበረም።

በአንጻሩ አሸባሪው ህወሓት ረሀብን እንደጦር መሳሪያ እየተጠቀመበት እንደሆነ፤ መኪናዎችን ያስቀረው ለጦርነቱ ሲል እንደሆነና በፌዴራል መንግስት ላይ ጫና ለማሳደር አስቦ መሆኑን ለእውነት የቆሙ ሁሉ ተረድተውታል።

ክእነዚህም መካከል የአሜሪካው ሲ ቢ ኤስ ጋዜጠኛ የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሄርሜላ አረጋዊ አንዷ ናት።

ሄርሜላ በወቅቱ አሸባሪው ቡድን ይህንን እየፈጸመ ያለው የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስትን በትግራይ ህዝብ ዘንድ ያለውን ተቀባይነት ለማሳጣት ሆን ብሎ የሚያደርገው መሆኑን አስታውቃ ነበር።

ዛሬም ሄርሜላ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርን የትዊተር መልዕክት ተቃውማ መልስ ሰጥታለች።

ተጨማሪ ያንብቡ:   ከአድዋ ድል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ቀን ድልም እንማር!!  - ከ ይሁኔ አየለ

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የመንግስትን ውሳኔ በመቃወም፤ ኢትዮጵያ ውሳኔዋን ትቀይር የሚለውን መልዕክታቸውን የተመለከተችው ሄርሜላ፤ ሰብአዊነት?” ስትል አጣጥላዋለች።

400 በላይ እርዳታ ጭነው ወደ ትግራይ ተጉዘው የነበሩ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መኪኖች ትግራይ ቀርተው ጦርነቱን ይበልጥ ለማቀጣጠል ጥቅም ላይ ሲውሉ ለሁለት ወራት ዝም አላችሁ፤ የትግራይ ታጣቂዎች ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በመግባት ሺዎችን ሲገድሉስ ምን አላችሁ ስትል ተችታለች።

ሄርሜላ አያይዛም፤ ይህ አካሄዳቸውም በአፍሪካዊያን ሕይወት ላይ መጫወት ነው ስትል የአንቶኒ ብሊንከንን ሀሳብ ነቅፋለች።\

(ኢ ፕ ድ)

2 Comments

  1. ይህች ፈርጥ ልጅ በመጨረሻ ከየት መጣች ያረጋዊ በርሄ ልጅ በፍጹም ልትሆን አትችልም መቼም። በተዘረፈ በሀገር ሀብት የተማሩ የትግሬ ልጆች አብረዋት ቢቆሙ ለነገሩ ብቻዋንም ትደንቃለች።

  2. Great Hermela!!

    Truth always prevail as bloodshed of innocent people knock every doors. Though many journalists are doing unfair and unethical press release, you genuine journalist what is the mission of US government on Ethiopia??? Really a mess they are doing.

    Regarding America it is not a surprise that seeing day and night about US wrong foreign policy in Ethiopia and a blind support for TPLF as this mission has been drafted quite many years back on bringing TPLF to power and aggressively working to dismantle Ethiopia by their divide and rule ethnic federalism.

    Anyways it is no the time for their deviling acts, Ethiopian government also has to be smart enough on each steps that has to be done since it is an issue of all Ethiopian people except their affiliates. PM Abiy has to investigate the mission of Ethiopian Ambassadors in some countries as still there are supporters of TPLF; like, US ambassador and some other countries, they are doing behind the curtain. Watch it!!! Urgent & serious actions needed.

    Long live to Ethiopia!!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share