አራት የቤተሰብ አባላቶቼ በአሸባሪው ቡድን በግፍ ተገድለዋል

242201506 3027814300794362 7415102565538590134 n

አሸባሪው የህወሃት ቡድን ደባርቅን ለመያዝ በፈጸመው ወረራ ” ቦዛ ” በተባለው ቀበሌ አራት የቤተሰብ አባላቶቼን በግፍ ገድሎ፤ በአንድ ጉድጓድ ቀብሯል ሲሉ አሜሪካ የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጅ ተናገሩ።

ትዕግስት አንጋው ይባላሉ፤ ከአሜሪካን መጥተው የአንድ ዓመት ዕድሜ ያለው ህጻን ልጃቸውን ጎንደር ከተማ ትተው ለ12 ቀናት በደባርቅ ግንባር ከሽብር ቡድኑ ጋር ከሚዋደቀው ሰራዊት ጋር (ቁመዋል) ፤ በማበረታታት ድጋፍ አድርገዋል።

የሽብር ቡድኑ በሰሜን ጎንደር ዞን ወቅን ጭና ቀበሌ የፈጸመውን አሰቃቂ ጭፍጨፋ በአካል ተገኝተው ተመልክተዋል።

የሽብር ቡድኑ በፍጹም ጥላቻ ተነሳስቶ የፈጸመው የዘር ጭፍጨፋ ከኢትዮጵያዊነት እሴቶች ያፈነገጠ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት መሆኑን ይገልጻሉ።

ህወሃት በስልጣን ዘመኑ ወንድሞቼን በእስር ከማንገላታቱም በላይ አንድ አጎቴንም በግፍ መግደሉ የጭካኔ ጥግ ማሳያ ነው ይላሉ።

ይሄ አልበቃ ብሎት ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ደባርቅ ለመያዝ በፈጸመው ወረራ “ቦዛ” በተባለው ቀበሌ አራት የቤተሰብ አባላቶቼን በግፍ ገድሎ በአንድ ጉድጓድ ቀብሯል ሲሉ በቁጭት ገልጸዋል፡፡

የህወሃት የሽብር ቡድን በህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለው ግፍና በደል ተዘርዝሮ እንደማያልቅ የተናገሩት ወይዘሮ ትዕግስት፤ የአካባቢው ህዝብ ከሰራዊቱ ጎን በመሰለፍ ያደረገው እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ በታሪክ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

የሴት ተዋጊዎች የውጊያ ሞራልና ብቃት ጉልህ ስፍራ እንዳለው ነው ወይዘሮ ትዕግስት የተናገሩት።

ለተዋጊ ሰራዊቱ ከ200 ሺህ ብር በላይ ወጭ የተደረገበት ብስኩት፣የዝናብ ልብስ፣ ውሃና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ማቅረብ እንደቻሉ አመልክተዋል።

ለሴት ተዋጊዎችም የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በማቅረብ የዜግነት ድርሻቸው ለመወጣት ጥረት አድርገዋል፡፡

በአውደ ውጊያዎች በጀግንነት ሲዋጉ የሚቆስሉትን የሰራዊት አባላት በመንከባከብ እንዲሁም ወደ ሆስፒታል በፍጥነት በማድረስ በኩል ከአካባቢው ህዝብ ጋር በመተባበር ድጋፍ ሰጥተዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  UN Expert Discusses Human Rights Violations in Ethiopia

”የአማራና የትግራይ ህዝቦች ረጅም ዘመናት ያስቆጠረ የአብሮነት እሴቶች ቢኖረንም የሽብር ቡድኑ ይህን ዘመናት የተሻገረ አብሮነት በማጥፋት በህዝቦች መካከል እልቂት እንዲፈጠር እየሰራ ነው ”ብለዋል፡፡

ጦርነቱ ኢትዮጵያውያን አንድ እንድንሆን ያደረገ፤ በሁሉም አውደ ውጊያዎች የታዘብኩት ነገር ቢኖር ህዝቡ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ሆኖ የሽብር ቡድኑን ሲፋለም ለማየት ችያለሁ ነው ያሉት፡፡

በአሸባሪው የህወሃት ቡድን ለተፈናቀሉ ዜጎችም ሆነ በግንባር እየተዋደቀ ለሚገኘው ሃይል ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በሚችለው አቅም ሊያግዝ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የተፈጸመውን ዘግናኝ ድርጊት ያወገዙት ወይዘሮ ትግስት፤ ሴት ዲያስፖራዎች በአለም አቀፍ መድረኮች ድምጻቸውን ከፍ በማድረግ የሽብር ቡድኑን ወንጀል ለማጋለጥ እንደሚሰሩ ነው ያስታወቁት።

በተለይም ውጭ ሀገር ሆነው የህወሃት የሽብር ቡድንን የሀሰት ወሬዎች በማናፈስ አለም አቀፉን ማህበረሰብ እያደናገሩ ያሉ ቅጥረኛ አክቲቪስቶችን ሴራ ለማክሸፍ ሀገር ወዳድ ዲያስፖራዎችን በማስተባበር ስራዎችን እንሰራለን ብለዋል።

የጎንደር ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ አቶ ቻላቸው ዳኜ ፤ ወይዘሮ ትዕግስት አንጋው ከአሜሪካን መጥተው ሰራዊቱን በግንባር ተገኝተው በማበረታታትና በመደገፍ በኩል የሴት ዲያስፖራዎች ግንባር ቀደም አርአያ ናቸው ነው ያሉት።

ዲያስፖራው ለህልውና ዘመቻው በገንዘብና በቁሳቁስ ጭምር እያደረገ ያለው ድጋፍ የሚበረታታ መሆኑን አውስተው፤ ወደፊትም ይሄው ተጠናክሮ እንዲቀጥል መልዕክት አስተላልፈፈዋል፡፡

የህወሃት የሽብር ቡድንን የሴራ ፖለቲካ በመረጃ ላይ ተመስርቶ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በማሳወቅ ረገድ የዳያስፖራው አስተዋጽኦ የላቀ በመሆኑ በዚህም የድርሻቸውን እንዲወጣ አመልክተዋል።

የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችና በውጭ የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች ለህልውና ዘመቻው በጥሬ ገንዘብና ዓይነት ከ170 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ማድረጋቸውን ከከተማ አስተዳደሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የማይካድራ ጥቃት - ከ740 በላይ ሰዎች ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ተጨፍጭፈው የተገደሉበት

መስከረም 07/2014(ኢዜአ)

1 Comment

  1. ወያኔ ከአማራ አማራ ለይቶ ይጠላል። የጎንደር ስም ሲነሳ ያንቀጠቅጠዋል። ለምን ለሚሉ መልሱን እናንተው ፈልጉ እላለሁ። ጭካኔው ከሰላማዊ ሰው ነው የጀመረው አሁንም በሰላማዊ ሰው ላይ ነው ጉብዝናው። የጭቃ ቤት አፍርሶ፤ ከብቶችን አርዶ በልቶ የቀሩትን በጥይት ሩምታ ገድሎ ሰብል በማበላሸት በቤት አለ የተባለ ነገርን ሁሉ ጭኖ ወደ ትግራይ የሚያጓጓዝ የሌቦች ስብስብ ወያኔ ነው። ከቋንቋው ውስጥ እንደ ውሃና ምግብ ከአፉ የማይለየው አማራ የሚለው ስም ነው። ትንሹም ትልቁም ለዘመናት በወያኔና በመሰሎቹ የተሰበከለት አማራ ጠላትህ ነው። አማራ ነው ለረሃብ ያጋለጠህ፤ ከአገርህ እንድትሰደድ ያደረገህ፤ የአማራ ገዢ መደብ ነው ኋላ ቀር ያደረገህ እየተባለ በውሸት ትርክት የተዘፈቀን ያን ህዝብና የወያኔ ቡድን ከዚህ እይታቸው ማጥራት ከቶ አይቻልም።
    ሰው ገድሎ ጉድጓድ ውስጥ በተናጠልም ሆነ በጅምላ መጣል የወያኔ የቀን ሙሉ ስራ ነው። ወያኔ ማለት የአውሬዎች ስብስብ ማለት ነው። በመኪና ገጭቶ በመግደል፤ መርዝ በማብላት፤ አፍኖ መሬት ውስጥ ከቶ በማሰቃየት፤ በመግረፍ፤ ጥፍር በመንቀል፤ ውሃ የሞላ ነገር በብልት ላይ በማንጠልጠል፤ በሴትና በወንድ ላይ ሶዶማዊ ጥቃት በመፈጸም የታወቁና የተካኑ ለመሆናቸው ዛሬ በህይወት ኑሮው ስንጠይቃቸው አይ ለሰው ጀሮም ይቀፋል አንናገርም በማለት ጉዳታቸውን ደብቀውና አካለ ስንኩል ሆነው የሚተነፍሱት ይመሰክራሉ። በሃበሻው የረጅም ጊዜ የመጠላለፍና የመኖር የፓለቲካ ስልት እንደ ወያኔ ሃርነት (ባርነት) ትግራይ ያለ የአረመኔዎች የፓለቲካ ስብስብ በምድሪቱ በቅሎ አያውቅም። ሃገርን ቆርሰው እንካችሁ የሚሉ የቀን ደላላዎች ናቸው። አሁን በጎንደር በወሎና በአፋር የምናየውና የምንሰማው ሰቆቃ ታልሞ፤ ታቅዶ፤ ተጠንቶ የተደረገ እንጂ ግጭቱ የፈጠረው የፓለቲካ ትኩሳት አይደለም። ግን የሚያሳዝነው የፌዴራል መንግስት ነኝ ባዪ ወያኔ ይህን ሁሉ ጉዳት እስኪያደርስ የት ነበር? ይገርማል አበው እንደሚሉት ሰዶ ማሳደድ ካማረህ ዶሮህን በቆቅ ለውጥ ነው።
    ዛሬ ለቅማንት ለአገው ለኦሮሞው ለአፋሩ ወዘተ ነጻነት ይገደናል የሚለው ወያኔ ልክ እንደ ጣሊያኖች ከፋፍሎ ለመግዛት እንዲመቸው እንጂ በስልጣን ዘመኑ ለእነዚህ አሁን ኑና እኔን ምሰሉ ለሚላቸው አጥፊ ሃይሎች ያደረገው አንዳች መልካም ነገር የለም። ወያኔ ድርቡሽ ነው። በሃገርና ከሃገር ውጭ ያሉ ተቃዋሚዎቹን ሁሉ ከፍሎ ያስገድላል። ለነጮች ከፍሎ ውሸትን በእውነት ያስለውጣል። ታዋቂ ሰዎችን እንዲከታተሉ ወይም እንዲገሉ ያደርጋል። ስልካቸውን ያሰርቃል ያን የተሰረቀም ስልክ በመከፋፈት ያለ የሌለ ነገሩን ጎርጉሮ በማውጣት ለፓለቲካ ሥራው ይጠቀምበታል። አዲስ አበባ ውስጥ በእስር ቤቶችን ሳይቀር በአውቆ አበዶች ከፍሎ ያስደበደባቸው ቁጥራቸው ብዙ ነው።
    አሁን የትግራይ ወጣት አለቀ፤ ትግራይ ተራበ፤ ገለ መሌ የሚሉን ሁሉ ከወያኔ የማይሻሉ ተልካሾች ናቸው። እንጀራ ከእጅህ ላይ ተቀብሎ በጥይት ደብድቦ ከሚገልህ ጠላት ጋር እንዴት ያለ እርቅና ርህራሄ ነው የምታደርገው? ከአማራ ህዝብ ጋር የምናወራርደው ሂሳብ አለን የሚሉ ጅሎች ጋር እንዴት ነው ሂሳብ የምታሰላው? ኢትዮጵያን ለማውደም ሲኦል ድረስ እንወርዳለን የሚሉ ሰዎች እንዴት ጤነኛ እይታ ይኖራቸዋል ብሎ ሰው ያስባል? ወያኔ የሚገባውና የሚነቃው ባሩድ ሲሸተውና በዚያው ጦስ ሲሰናበት ብቻ ነው። እሳትን በእሳት መፋለም እስካልተቻለ ድረስ ንፋስ የበተነው የፊኖ ድቈት ሆነ የተባለው ወያኔ ነው ዛሬ አፋር ድረስ ዘልቆ የሰውን ሰቆቃ ጣራ ላይ ያደረሰው። መደራጀት፤ መታጠቅ፤ መተባበር፤ በአንድ እጅ ማረሻ በሌላው ጠበንጃ ይዞ የራስንና የሃገርን ሰላም ለማስጠበቅ መፋለም ምርጫ የማይገኝለት ብልሃት ነው። እናስብ ወያኔ ሮኬት የተኮሰው አስመራና አማራ ክልል ላይ ነው። ለምን?
    የእርዳታ እህል አልገባ አለ በሩ ተዘጋ እያለ የሚያላዝነው ይህ የሙት ስብስብ እርዳታ ሊያደርሱ የተላኩ መኪናዎችን ቀምቶ ያስቀረ ሽፍታ ነው። ወያኔ ማለት ወሮ በላ ማለት ነው። ይባስ ብለው ነዳጅ ስለሌለ ነው ያልተመለሱት ይሉናል። ወያኔ እውነትነት ያለው ነገርም ቢናገር የሚያምነው ማንም የለም። ለዚህም ነው ወያኔ የወራሪና የዘራፊ ሃይል ነው የምንለው። ድሮም ለ 27 ዓመት የሃገሪቱን አንጡራ ሃብት ሲዘርፉ ኖረው ዛሬም ባንክና የግል ቤቶችን እቃ እየጫኑ መቀሌ መውሰዳቸው ከሽፍትነት ወደ ተራ ቀማኛነት መተላለፋቸውን ያሳየናል።
    ወያኔ እኮ የውሸት ብር አትሞ ህዝቡንና ራሱን የሚያታልል ቡድን ነው። ግን የደነዘዘው የአብይ መንግስት ይህንና መሰል ሰቅጣጭ የወያኔን ጨካኝነት ለምን ለአለም ህዝብ በግልጽ እንደማያሳውቅ ሊገባኝ አይችልም። ለምሳሌ ከተመድ ግዳጅ አንመለስም በማለት መሬት ላይ ወድቀው ተንከባለው አሁን በሱዳን የስደተኞች ሰፈር ወታደራዊ መልማይና አሰልጣኝ ስለሆኑት ሰዎች በዝርዝር ማን ማን እንደሆኑ በዓለም ላይ ለተበተነው ህዝባችንና ለሃገር ቤቱም ማስታወቅ ነበረባቸው። ዛሬ በትግራይ ተወሽቀው ጦርነቱን የሚመርቱን የወያኔ የቀድሞ የሲቪልና የወታደራዊ ባለስልጣኖች ሃብትና ንብረት መንጠቅ ሲገባ አሁንም ከዚያው የሚመነጨው ብርና ዶላር ነው ሃገሪቱን እያመሰ ያለው። ከዚያም በላይ ከ 40 ዓመት በላይ የዘረጋውን የስለላ መረብ፤ ህገ ወጥ የሆነ የገንዘብ ዝውውር ማምከን ሲቻል ሁሌ ማይክሮፎን ይዞ መለፍለፍ የቀን ተቀን ጉዳይ ሆኗል። ሽለላው፤ ድንፋታው፤ ሃገር ትፈርሳለች አትፈርስም እያሉ መነታረኩ ቢቀር ይሻላል። በጠላት ላይ ድል ለማግኘት የስለላ ፍሬና መረጃውን ተመርኩዞ በፍጥነት ማጥቃት ለወታደራዊ ግዳጅ ወሳኝ ናቸው።
    ባጭሩ ወያኔ የአማራን ህዝብ ለማጥፋት የተነሳው ዛሬ ሳይሆን ገና ከጅምሩ ነው። በወልቃይት ጸገዴና ጠለምት በሌሎችም በጉልበት የትግራይ ክልል ባደረጋቸው አካባቢዎች ይህ ነው የማይባል ከናዚ ጀርመን ገስታፓ የሚወዳደር ወንጀል ፈጽመዋል። የኢትዮጵያን ባንዲራ በመያዙ እጅ የተቆረጠ ወጣት አለ። መሰደድ፤ መገደሉ፤ መሬታቸውንና የቀንድና የጋማ ከብቶች መቀማታቸው፤ ከቀያቸው መፈናቀላቸው ታሪክ መዝግቦ የያዘው ነው። ወያኔ ትግራይን ገንጥሎ በራሱ መንግስት ሆኖ መኖር ካማረው ይገንጠል። ግን ወያኔ እያለ ምስራቅ አፍሪቃም ሆነ ከቁራሽ ተራፊዋ ኢትዮጵያ ሰላም አይኖራትም። ስለሆነም ተፋልሞ ማለፍ እንጂ ለወያኔ እጅ መስጠት ጭራሽ አይታሰብም። ሞት ለወያኔ! በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share