” ማነው የተካደው ?! ” በሰርካለም ፋሲል – ግርማ ካሳ

(ሰርካለም ፋሲል የእስክንድር ነጋ ባለቤት ናት፡፡ እርሷም እንደ እስክንድር ጋዜጠኛ ነበረች፡፡ በ97 ሰባት ከቅንጅት መሪዎች ጋር አብረው ለሁለት አመት ከታሰሩ ጋዜጠኞች መካከል እርሷና ባለቤቷ እስክንደር ነጋ ይገኙበት ነበር፡፡ እስር ቤት እያለች ነፍሰ ጡር ስለነበረች እዚያ እያለች ነበር አንድና ብቸኛ ልጃቸውን ናፍቆት እስክንድርን የወለደችው)

240602857 10225874007467596 7040496970008485619 nአንዳንዶች እስክንድር በጎደኞቹ ‘ተክድዋል’ ሲሉ ይደመጣሉ። ዕውነት እስክንድር ተክድዋል ????

በእኔ አስተሳሰብ እስክንድር አልተካደም። ክህደት ካለም ከሃጂው ህሊናውን ፣ዓላማውን፣ ትግሉን ራሱን ነው የከዳው።
ትላንት ህገ-መንግሥቱ አይወክለንም ስትል ከርመህ፣ ዛሬ ምንም ማሻሻያ ያልተደረገበት ህገ- መንግሥት ይወክለኛል ካልክ እስክንድር ሳይሆን፣ ዓላማህን፣ ትግልህን ራስህን ክደህዋል።
ትላንት ኤምባሲዎች በሙሉ የወያኔ ናቸው ማንም ሰው እንዳይገባ ብለህ ስትቀሰቅስ ፣ ዛሬ ስብሰባ እና ጭፈራ ስታካሄድበት-እስክንድርን ሳይኾን፣ ዓላማህን፣ ትግልህን ራስህን ነው የካድከው።
ትላንት የአንድን ዘር የበላይነት ስትቃወም፣ ዛሬ የአንድ ዘር የበላይነት ከተቀበልክ እስክንድርን ሳይሆን ትግሉን ፣ ዓላማህን፣ ራስህን ክደኸዋል።
ትላንት የፍትህ ተቁሙን ፣ የፀረ-ሽብር አንቀፁ ፣ህገ-ወጥ እስር፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱን፣ በመቃወም ድምፅህን ስታሰማ ኖረህ፣ ዛሬ የሰው ልጅ በአደባባይ አካሉ ሲቆራረጥ፣ ንፁሃን ትላንት በተቃወምከው የህግ አንቀፅ ተከሰው ወህኒ ሲወረወሩ ዝምታን ከመረጥህ የከዳኸው እስክንድርን ሳይኾን ራስህን ነው። የከዳኸው ሰምቶ እንዳልሰማ ዓይቶ እንዳላየ ዝምታን የመረጠው ህሊናህን እንጅ እስክንድርን አይደለም።
ትላንት ሕወኃትን ስትቃወም ፅድቅ፣ የሕወኃት የአንድ ሳንቲም ግልባጭ ኦህዴድን ስትቃወም ወንጀል ከሆነ የከዳኸው እስክንድርን ሳይኾን ትግሉንና ራስህን ነው።
አዎ …ግን ደግሞ እስክንድር ተክድዋል። ክህደት የምለው፣
ትላንት እስክንድርን፣ እንደመታገያ ስልት ተጠቅመው ስሙን ሲያነሱ የነበሩ፣ ዛሬ እስክንድር ያልተናገረው የተናገረ በማስመሰል ‘ካልታሰረ’ ብለው ማመልከቻ እስከ ማስገባት(ማመልከቻው ግነት ነች) የደረሱ፣ አለፍ ብለውም፣’ህብዕ’ ሲሉ ለዐቃቤ ህግ የክስ ማጠናከሪያ እስከመኾን የተጉዋዙ ነበሩ። ለእኔ ክህደት ይህ ብቻ ነው። ሰውን በሃሰት መወንጀል። ለዚያውም ጥንቅቅ አድርገህ የምታውቀውን። ከእጁ የበላህ የጠጣኸው። (ጌታው ዐቃቤ ህግ በምስክር ድርቅ ተመትዋል እኮ ያቺ ፌስቡክ ላይ የለጠፍካትን በአካል ቀርበህ ብትመሰክር ስል…ሃሳብ አቀረብኩኝ።)
:
ትላንት…….. ብዙ ማለት ይቻላል ወ.ዘ.ተ ብለን ካላለፍነው።
እስክንድርማ ትላንት በጋዜጠኝነቱ ፣ ዛሬም በፖለቲከኝነቱ ፣ ፍትህ ተጎደለ ደሃ ተበደለ ብሎ ድምፁን ከማሰማት አልተቆጠበም። እስክንድርማ ላመነበት መስዋዕት መክፈሉን ዛሬም አላቆመም። እናም… እስክንድር ተክድትዋል አትበሉኝ። የተካዳካዳችኹ ካላችኹ ተጠያየቁ። ለእኔ፣ እስክንድር ዓላማ አለው። መነሻና መድረሻውን ያውቃል። ዳገት ላይ ሸብረክ አላለም። አቁራጭ መንገድ ፈልጎ ርምጃውን አልገታም። ጉዞ ላይ ነው።
በመጨረሻም እንደኔ ፍላጎት ምርጫው ቢሆን(እመኛለሁ) አሜሪካ ቢኖር። በተለይ፣ ለእስክንድር ይመቸዋል። አይደክምም፣ አይጎሳቆልም፣ አይከሳም አይጠቁርም። በቀላሉ፣ እጅግ በቀላሉ ዘና ብሎ፣ መኖር የሚያስችለው ብቃት አለው። ፈጣሪ ፀሎቴን ይስማ!!!
የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ!!!
ሰርካለም ፋሲል ( የእስክንድር ነጋ ባለቤት
ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን መግለጫ

5 Comments

  1. ውድ ሰርካለም ፋሲል፣
    የደረሰብሽን ጒስቊልና እዚህ መዘርዘር አያሻኝም።
    ስለ እስክንድር ግን ሚስቱ ስለ ሆንሽ ከቅርብ ያልታየሽ ነገር አለ።
    ይኸውም እስክንድር ደፋር ይሁን እንጂ፣ ድፍረቱ ከትክክለኛ መረጃ እና
    ከአርቆ ማስተዋል ጋር ስላልተቆራኘ፣ ያልተገባ ሥቃይ ውስጥ ገብቷል።
    እውነቱን እንነጋገር ካልን እስክንድር የፖለቲካ ሰው አይደለም። ልክ እንደ ፕሮፌሰር ኣሥራት።
    እንደ እኔ እንደ እኔ “አሜሪካ ቢኖር” ባልሽው ግፊበት፤
    የሰላም ዓመት ላንቺ እና ለቤተ ሰብሽ ሁሉ እመኛለሁ።

  2. Ato Alem W/ro Alem Ewnetegna sew poletikegna ayihonim Le malet New ????n Tadiya chigrachin Poletikawn Kettafiwoch Sileyazut new Chigrachin Alalik Yalew ende Eskinder nega yalu Ewunetegna sewoch binoru Chigir balihone neber

    • ውድ በለው፣
      ያልኩትን አንብበህ የተረዳህ አይመስለኝም፤ እስክንድር ደፋር እና የማያስተውል ነው፤ የሚመክረው አላገኘም፤ ምክር የሚቀበል አይደለም። አሁንስ ግልጽ አልሆነልህም?

  3. WID SERKALEM YEDERESEBISHIN YELIB HAZEN EGARAWALEHU . LIJISHIM LEZIH YAHIL ZEMEN YEABATUN FIKIR BALEMATATAMU YISEMAGNAL.
    DEAR SERKALEM.
    ESKINKDI NEGA LENETSNET YEKEFELEWIN WAGA SALADENK ALALFIM . EGZIABHER KE ESIRAT ENDIFETAW ETSELIYALEHU .
    WEDE WANAW MELKITE SIMETA ESKINDIR NEGA POLETIKEGNA MEHON YEMICHIL SEW AYMESLEGNIM . POLETIKEGNA SITIHOGNI BIZU NEGEROCHIN EYAWEKSHI NEGEROCHIN YEMITIGELCHIBET GIZENA HUNETAN TAMECHACHALESH ESKINDIR GIN ENDEZA AYDELEM . HULUM NEGER GILTS NEW . POLETICA DEGMO BIZU GILTSINET AYFELIGIM. AND GIZE JAWAR MOHAMMED YALEWIN KESEMAHU BEHWALA NEW ESKINDIR MIN YAHIL YEWAH ENDEHONE YEGEBAGN . MIN ALE MESELESH ” ENE SILE AND GUDAY LEMENAGER MINIM AJENDA AYASFELIGEGNIM AGENDAWIN KE ESKINDIR AGEGNEWALEHU . NEGE MIN MESRAT ENDASEBE , SEBSEBA LAY MIN ENDEWESENU KESU AF SILEMISEMA LENE ESKINDIR YIMECHEGNAL ” NEW YALEW .
    HULUM NEGER FIT LEFIT NEBER YEMIGAFETEW YA DEGMO HAGERU ESAT EYENEDEDEBAT BALECH HAGER TINISH NEGEROCHIN LEZEB YEMYADERG NEGER YASFELIG NEBER ENJI ESKINDIRIN MAN YITELAL? YAWIM LEGNA NETANET RASUN MESWAET LADEREGE .
    AHUNIM ENE YEMIMEKIRISH GUDAY BINOR ESKINDIR MEFETATU AYKERIM ENAM SIFETA YETEWESENE GIZE KENANTE GAR EREFIT BIYADERG KELIJUM GAR HONO YETEWESENE GIZE BIYASALIF TIRU YIMESLEGNAL . LESUM TIDARUN YEMATATAMIA GIZE YASFELIGEWAL.

  4. ሰርክ አለም ነች ወይ የጻፈችው በዚህ ጥልፍልፍ ተንኮለኛ አካሄድ ትግሬዎችና የአብይ ሰዎች ስለረቀቁበት ነብሱን ለሀገሩ የሰጠውን አናብጠለጥለው እንዲችሉ አይነት አካሄድ አማራው ከምድረ ገጽ ሊጠፋ ሲቃረብ ሲያጨበጭቡ የነበሩ ዛሬ ተደራጅቶ አትግደሉኝ ሲል አማራውን ዘረኛ ሆነ ብለው እንደሚያሾፉት አይነት ነውና እስክንድር ያልሞከረው የለም የኢትዮጵያ ጠላቶች ዙሪያውን ስለከበቡት እፕማራጩ እስክንድር የወሰደው ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share