ታሪክን ጠብቆ ማለፍ ክብር ነው፣ ታሪክ ሠርቶ ማለፍ ደግሞ እንደመታደል ይቆጠራል። እንደ ታጋይ ሠረበ በየነ ተዓምር የሠራ ሲገኝ ግን አጃኢብ ከማለት ውጪ ከትቦ ለማስነበብም ሆነ ተናግሮ ለማሳመን ይቸግራል። ታጋይ ሠረበ በየነ ኢትዮጵያዊነትን ከደምና ከአጥንቱ ካዋሃደው የአማራ ሕዝብ አብራክ የወጡ ጀግና ናቸው።
እስከ 1984 ዓ.ም ጫካ ገብተው ባደረጉት ትግል ሀገሪቱን ለመከራ ሕዝቡንም ለባርነት አስቦ በተንቀሳቀሰው ተገንጣይ ኀይል ላይ ከፍተኛ ቁሳዊና ሰብዓዊ ኪሳራ አድርሰዋል። የነበረውን የመሳሪያ እጥረትም ጠላትን በመማረክ ማሟላት ችለዋል። ከዚያም ወደ ኤርትራ በርሃ አቅንተው ትግላቸውን ሲቀጥሉ ነሐሴ 25/1986 ዓ.ም በአሸባሪው የትህነግ ታጣቂዎች ታፈኑ።
አቶ ታዲዮስ ታንቱ በ80 አመታቸው እንክብካቤ እንጅ እስር አይገባቸውም መታሰር ያለባቸው ብዙ ባንዳዎች እያሉ የሳቸው መታሰር ኢፍትሀዊ ነው