ታዋቂነት እኮ ሁሉን ማወቅ ማለት አይደለም! – ጠገናው ጎሹ

August 30, 2021
ጠገናው ጎሹ

ታዋቂነት (prominence/popularity)) ግለሰቦች ወይም ቡድኖች በተሠማሩባቸው የሙያ ፣የእውቀት ፣ የክህሎት ፣ የማህበራዊ አገልግሎት ፣ ወዘተ መስኮች በአንፃራዊነት (በገሃዱ ዓለም ፍፁም የሚባል ነገር የለምና) ልዩ የሆኑ አወንታዊ አስተዋፅኦዎችን በማበርከታቸው የሚ ያገኙት መጠሪያ ቅፅል ነው ።

famousእውነተኛ ታዋቂነት እራስን በሁሉም ነገር (ጉዳይ) አዋቂና ሁልጊዜም ትክክል አድርጎ ከማሰብ  እጅግ እንጭጭና የተሳሳተ አስተሳሰብ (very infantile and wrong way of thinking) ጋር ጨርሶ ግንኙነት የለውም። እንዲያውም በተቃራኒው እውነተኛ ታዋቂነት ማለት ለሚደረጉ ንግግሮች አስፈላጊውን ትኩረት ወይም ጥንቃቄ የማድረግ እና ሊከሰቱ የሚችሉ ስህተቶችን  በፀጋ ተቀብሎ ለመታረምና ለማረም ሃላፊነነትን ለመውሰድ የሚያስችል ባህሪን  የተላበሰ ሰብእና ነው።

ከዘመን ጋር አብረን እንድንዘምን የሚያስችሉንን ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ፣ ባህላዊ፣ ሥነ ልቦናዊ ፣ ሥነ ምግባራዊ ፣ ሞራላዊ ፣ ወዘተ ሁኔታዎች መሠረታዊና ዘላቂ በሆነ አካሄድ ለመፍጠርና ለማዳበር ባለመቻላችን የታዋቂነት ትርጉምና እሴት በሁሉም ነገርና ሁልጊዜም ትክክል ከመሆን እጅግ የተሳሳተ አስተሳሰብ ጋር  እየተደበላለቀብን ተቸግረናል።  አብዛኛዎቹ ታዋቂዎቻችንም በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የዚሁ አይነት አስተሳሰብ ሰለባዎች ናቸው በሚለውን ሂሳዊ አስተያየት እንደ ድፍረት ወይም እንደ ክብረ ነክ ወይም እንደ ነውር በመቁጠር አካኪ ዘራፍ (ያዙኝና ልቀቁኝ) ከማለት  ክፉ አባዜ ለመውጣት ከእራሳችን ጋር እና በመካከላችን እልህ አስጨራሽ ጥረት ማድረግ ይኖርብናል።

የሩብ ምእተ ዓመቱ የመከራና የውርደት ፖለቲካ ሥርዓት ወደ መማሪያ ታሪክነት ተለውጦ   እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን ይሆናል ስንል በዚያው ሥርዓት ውስጥ በባሰ ሁኔታ ተመልሰን ከተዘፈቅንባቸው ዋነኛ ምክንያቶች አንዱ በምሁርነቱ (intellectualism) ፣ በኪነ ጥበቡ (art) ፣ በፖለቲካ/በማህበራዊና በሰብአዊ መብቶች አንቂነቱ (activism) ፣ ወዘተ ዘርፍ ያገኘነውን ታዋቂነት የሥርዓትን ለውጥ እውን ከማድረግ ጥያቄ ጋር ሳይሆን  ከህወሃት መወገድ ጋር  ብቻ  ማያያዛችን እና ታዋቂነትን  እጅግ ከተሳሳተ ሁሉን የማወቅ አስተሳሰብ ጋር  እያደበላለቅን የስሜታዊነት ፖለቲካ ሰላባዎች የመሆናችን እውነታ ነው።

ባሳለፍነው የአውሮጳዊያን ወር መጨረሻ (July 31, 2021) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የወቅቱ ተመራቂ ተማሪዎቹን ማስመረቁ ይታወሳል። ዩኒቨርሲቲው ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ከታዋቂ የሙዚቃ (የኪነ ጥበብ ዘርፍ) ባለሞያዎች አንዱ ለሆነው ለቴዎድሮስ ካሳሁን የክብር ዶክትሬት መስጠቱም ይታወሳል።

እንደ እኔ ግንዛቤ ወይም አረዳድ የእለቱ ዝግጅት በጥቅሉ ሲታይ ፦

ሀ) ተመራቂዎቹ የከፍተኛ ትምህርታቸውን አጠናቀው ለመመረቅ መብቃታቸውን በደስታ የማብሠር ፣ በተግባር ወደ የሚፈተኑበት የህይወት ምእራፍ እየተሸጋገሩ መሆናቸውን  የማስገንዘብ እና ይህንኑ በአግባቡ ተረድተው በተለይ አገራቸው ከምትገኝበት የወቅቱ  ግዙፍና መሪር እውነታ አንፃር  አስፊላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ የማስገንዝብ ፤

ለ) ለቅድመ ምረቃ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች፣ በየትምህርት ደረጃው ለሚገኙ ሌሎች  ተማሪዎች ፣ አሁን እድሉ ባይገጥማቸውም ወደ ፊት ለመማር ዓላማና ፍላጎት ላላቸው ወገኖች እና እንዲሁም ልጆቻቸውን እያስተማሩ ላሉና ለማስተማር ለሚፈልጉ ወላጆች  “እኛም እንችላለን” የሚል  የበጎ ተስፋ ስሜት የማሳደር ፤ እና

ሐ) የኪነ ጥበብ ሙያ አንዱ ዘርፍ  በሆነው የሙዚቃ ባለሙያነቱ የአገርን ታሪክ ፣ ባህል፣ ወግ ፣ ፍቅርና አንድነት አጉልቶ በማሳየት ረገድ  የህዝብን አድናቆት  (popuparity) ካተረፉት መካከል አንዱ ለሆነው ለቴዎድሮስ ካሳሁን የክብር ዶክትሬት (honorary degree) በመስጠት በዚሁ ዘርፍ ለተሰማሩ ወይም ለመሰማራት ጥረት እያደረጉ ላሉ ወገኖች በጎ ተፅዕኖ የማሳደር  ቁም ነገሮችን  የያዘ ነበር ማለት ይቻላል።

ይሁን እንጅ ዝግጅቱ መከረኛው ህዝብ ለዘመናት የመጣበትንና አሁንም በሸፍጠኛ፣ ሴረኛና ጨካኝ የኢህአዴግ ውላጅ ገዥ ቡድኖች ሥር መከራና ውርደቱን እየቆጠረ ያለበትን ግዙፍና መሪር ሃቅ በሚመጥን ሁኔታ አንፀባርቋል ማለት አይቻልም።  ይህ ማለት ግን ዝግጅቱ የፖለቲካ መድረክ መሆን ነበረበት ማለት አይደለም። የትምህርት ትክክለኛው ትርጉምና እሴት ማህበረሰብ የሚያጋጥመውን ተፈጥሯዊም ሆነ ሰው ሠራሽ አደጋ (catastrophe) ሲሆን ቀድሞ መከላከል ካልሆነም ቀድሞ በመድረስ መታደግ ከመሆኑ አንፃር እና ኢትዮጵያም እጅግ ፈታኝ በሆነ አጠቃላይ ቀውስ ውስጥ የምትገኝ ከመሆኗ  አንፃር  ከዝግጅቱ ብዙ ሲጠበቅ የተጠበቀውን ያህል አለመሆኑ ን መግለፅ ዝግጅቱን ማኮሰስ ተደርጎ ሊታይ አይገባም።

የዝግጅቱ አጠቃላይ ድክመት አልበቃ ያለ ይመስል ጭራሽ በመሬት ላይ ያለውን የጎሳ/የጎጥ/የቋንቋ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ቁማር መሪር እውነታ “… በስብሶ ተቀብሯል” በሚል ቅዠታዊ (dellusional) ዲስኩር  ሲገለፅ መስማት ሚዛናዊ ህሊናን ይኮሰኩሳል ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የመርህ  አልባነት ፖለቲካችንና አስከፊ ውጤቱ - ጠገናው ጎሹ

የአስተያየቴ ትኩረት ቴዎድሮስ ካሳሁን ባደረጋት አጭር ዲስኩር (ንግግር) ውስጥ ስለታዘብኳት የንግግሩ ክፍል በመሆኑ እንጅ ከዚያ ባሻገር ሂሳዊ ትችት በሚያስፈልጋቸው ወይም ጥያቄ በሚያጭሩ ጉዳዮች ላይ ብዙ ማለት ይቻላል።

ለምሳሌ ፦

  • እጅግ ሃላፊነት በጎደለው የሥርዓቱ ካድሬዎችና አድርባይ ምሁራን ምክንያት ላለፉት ሦስት ዓሥርተ ዓመታት በእጅጉ ከተጎሳቆለው እና አሁንም በባሰ አኳኋን ከቀጠለው የትምህርት ፍልስፍና እና ፖሊሲ አንፃር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እያተሙ የሚያድሏቸው የላቀ ትምህርት ደረጃ እና የላቀ የሙያ አስተዋፅኦ የምሥክር ወረቀቶች ትውልድን በመቅረፅ ረገድ ምን ያህል ተሳክቶላቸዋል? የመደበኛ ትምህርትና የክብር ዶክተርነት መመዘኛዎቻቸውስ የገሃዱን ዓለም ችግር ለመፍታት ካላቸው ብቃትና ዝግጁነት አንፃር ምን ያህል የተፈተሹ፣ አስተማማኝና የተዋጣለቸው ናቸው? ወዘተ ብሎ መጠየቅ ነውር ወይም ክብረ ነክ ወይም ስም አጥፊነት ከቶ ሊሆን አይችልም።
  • ቴዎድሮስ ካሳሁንን በተመለከተም በሙዚቃ ባለሙያነቱ ለአገር ያበርረከተው እጅግ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደ ተጠበቀ ሆኖ የኢህአዴግ አንጃ የሆኑት የጎሳ ፖለቲካ ቁማርተኞች “ዴሞክራሲያዊ ተሃድሶ” በሚል በመከረኛው ህዝብ ላይ በሚሳለቁበት በዚህ እጅግ አስቸጋሪ ወቅት  ምን ተናገረ ወይም ምን አይነት የዴሞክራሲያዊ አርበኝነት መልእክት አስተላለፈ?  ለመሆኑ ቤተ መንግሥቱን በተረኝነት የተቆጣጠሩትን ኢህአዴጋዊያንን (ብልፅግናዊያንን) ጨምሮ በሸፍጠኛና ሴረኛ የጎሳ ፖለቲካ ቁማርተኞች ምክንያት አገር ከሦስት ዓመታት በላይ ለንፁሃን ዜጎቿ ምድረ ሲኦል ስትሆን በሙያውም ይሁን በሌላ የመልእክት ማስተላለፊያ ዘዴ (መንገድ) ምን መልእክት አስተላለፈ? በሙያው ያሽሞነሞነው ህዝብ እና ያሽሞነሞናት አገር በዓላማ ሳይሆን በቤተ መንግሥት ዙፋን እና በአገር አንጡራ ሃብት ዝርፊያ ዙሪያ በሚተናነቁ ኢህአዴጋዊያን አንጃዎች ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ አኳኋን ምስቅልቅሏ ሲወጣ በየትኛው አደባባይ ወይም የመገናኛ መድረክ  ወጥቶ  ምን ተናገረ? ምንስ አደረገ? ብሎ መጠየቅ ከቶ ነውር ወይም ክብረ ነክ ወይም ስም አጥፊነት ወይም ጭፍን ጥላቻ ፣ወዘተ ሊሆን አይችልም። “የገንዘብ እርዳታ ስላደረገ ወይም እያደረገ ስለሆነ ከቃል ይልቅ ድርጊቱ ይመሰክርለታል” የሚል መከራከሪያ የሚያቀርቡና “እንደ ቴዎድሮስ ካሳሁን አይነት ታዋቂዎቻችን ለቀቅ” የሚሉ ወገኖች ሊኖሩ እንደሚችሉ በሚገባ እረዳለሁ። ስሜታቸውንም እረዳለሁና አይገርመኝም ።

ለዚህ ያለኝ አጭርና ግልፅ ምላሽ የሚከተለው ነው። በምንም መክንያትና የትም ይሁን ለተጎዱ ወገኖች ሁሉ የገንዘብና የማቴሪያል ድጋፍ የማድረግ አስፈላጊነት አያጠያይቅም። ይህ ግን የመከራውና የውርደቱ ዋነኛ ምክንያት የሆነውን ብልሹና ጨካኝ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ከማስወገድ እና እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እውን ከማድረግ ጋር በጥብቅ  ካልተያያዘ (ካልተቆራኘ) በእራሱ  ብቻ ከአስከፊው ሃዘንና መከራ ከቶ አያስጥለንም ወይም አይገላግለንም። አዎ!  የሰበብ ድሪቶ በመደረት የመከራና የሃዘን ምንጭ ከሆነው አስከፊ ኢህአዴጋዊ (ብልፅግናዊ)  ሥርዓት ጋር እየተሻሸን (እየተላላስን) እና ቆመን እያስገደልንና  እያጋዳደልን  የምንሰጠውን የሃዘን ወይም የማስተዛዘኛ ሳንቲም እንደ ትልቅ ገድል ወይም መስዋእትነት ወይም እንደ ስም መጠሪያ የምንቆጥር ከሆነ አደገኛ አስተሳሰብ ነውና ቆም ብለን ከምር ማሰብን ይጠይቀናል ።

 

ታዋቂዎቻችን የታዋቂነታቸውን ልኬታ በሚመጥን ሁኔታ ለአድናቂው ህዝብ (ለአገራቸው) የሚጠበቅባቸውን የዜግነት ሃላፊነት እንዲወጡ የሚያስችል ሂሳዊ ድጋፍ (critical support or offering support but with critique ) ስለ አላስለመድናቸው ሊነግሩን የሚፈልጉት  መከረኛው ህዝብ ቀን በቀን እየኖረበት ያለውን ግዙፍና መሪር ሃቅ ሳይሆን በምናባቸው የሚፈጥሩትን ግልብ ስሜትን ኮርኳሪ ፣ የተሳሳተና አሳሳች ዲስኩሮቻቸውን ነው። ለዚህም የሚቸራቸውን (የሚያገኙትን)  ጭብጨባና ጩኸት እንደ የታዋቂነታቸው ማረጋገጫ አድርገው ቢቆጥሩት ያሳስብ እንደሆነ  እንጅ ከቶ የሚገርም አይሆንም።

እንዲህ አይነቱ እጅግ ግልብና የተሳሳተ ዲስኩር ስሜታዊ የፖለቲካ ትኩሳት የሚንጠው ጭብጨባና ጩኸት ሲበረከትለት (ሲቸረው) መታዘብ ለዘመናት ከመጣንበትና አሁንም በባሰ ሁኔታ እንዲቀጥል ከተደረገው የመከራና የውርደት ሥርዓተ ፖለቲካ ለመውጣት የሚጠብቀን ፈታና እጅግ ከባድ መሆኑን ነው የሚነግረን።

“በዚያ የቴዎድሮስ ካሳሁን ለስሜት የሚስማማ (የሚጥም) ንግግር  አለማጨብጨብና አለመጮህ አስቸጋሪ ነበር” የሚል መከራከሪያ አስተያየት ሊነሳ እንደሚችልና መነሳቱም ተገቢ እንደሚሆን እረዳለሁ። እንዲህ አይነት በስሜት ፈረስ የሚያስጋልቡ ሁኔታዎችን ጨርሶ ማስወገድ ስለማይቻል ትናንትም ነበሩ፣ ዛሬም አሉ፣ ነገም ይኖራሉ ። የእኔ ትችታዊ አስተያየት እንዲህ አይነት አጠቃላይ እውነታዎች ለምን ኖሩ ወይም ይኖራሉ? የሚል አይደለም። የእኛ የፖለቲካ እውነታ ከዚህ አይነት አጠቃላይና ጨርሶ ማስወገድ ከማይቻለው እውነታ አንፃር ሲፈተሽ በእጅጉ ልኩን ያለፈና ከተሞክሮ ተምሮ ተገቢውን እርምት ከማድረግ ይልቅ እያደር እየተበላሸ የሚሄድ ክፉ ልማድ ነውና ሊያሳስበንና የሚበጀውን እርምት እንድናደርግ ግድ ሊለን ይገባል የሚል ነው። አዎ! ከሦስት አሥርተ ዓመታት እጅግ መሪር ተሞክሮ በኋላም እራስን እዚያው ክፉ አባዜ ውስጥ ማግኘት በእጅጉ ሊያሳስበንና ዛሬውኑ የሚበጀውን እርምት እንድናደርግ ሊያስገድደን ይገባል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ለመታደግ ከተፈለገ……..ፊልጶስ

ይህ አይነት የዲስኩሩን (የንግግሩን) ፍሬ ሃሳብ ሳይሆን ደስኳሪው (ተናጋሪው) በተወሰነ የሙያ መስክ ያገኘውን ታዋቂነት (popularoity) ሁሉንም እንደማወቅ አድርጎ በመውሰድ ልጓም በሌለው የስሜት ፈረስ የመጋለብ ክፉ ልማድ አንድ ቦታና ጊዜ ላይ መታረም ይኖርበታል።    አዎ! በዚህ አይነት የተደጋገመ ክፉ ልማድ ላይ ወቅታዊና ውጤታማ እርምት እስካላደረግን ድረስ ፖለቲካ ወለድ ወንጀል ለሚያስከትልብን አስከፊ ሃዘን የሃዘን መድረሻ (ማስተዛዘኛ) ሳንቲምና ቁሳቁስ እየለመንና እያስለመን እና እንደ አኩሪ ታሪክ እየተረክንና እያስተረክን እንቀጥላለን።  አዎ! የሥርዓት ለውጥ ጨርሶ በሌለበት ፖለቲካዊ እውነታ ውስጥ ከዚያኛው ወይም ከዚህኛው ግለሰብ ፖለቲከኛ ወይም ከእነዚህ ወይም ከእነዚያ የፖለቲካ ቡድኖች ርካሽ የፖለቲካ ጨዋታ ጋር ዥዋዥዌ እየተጫወትን አንዴ የመሪር ሃዘን ሙሾ ማውረድና ምፅዋእት መለመን እና ሌላ ጊዜ ደግሞ ሃዘኑና መከራው ታዋቂ በምንላቸው ወገኖች  ዲስኩር  እንደ ጉም ተኖ የጠፋ ወይም የሚጠፋ እስኪመስል ድረስ በጭብጨባና በጩኸት ጮቤ የመርገጥን (ልክ በሌለው የስሜት ትኩሳት የመጋለብን) ክፋ ልማድ ቆም ብለንና ልብ ገዝተን ልናጤነውና ወደ ትክክለኛው አስተሳሰብና አካሄድ ልንመልሰው ይገባል።ያለዚያ ለመጭው ትውልድ የምናስተላልፈው ይህንኑ አስከፊ የፖለቲካና የሞራል ጉስቁልና ይሆናል።

የገንዛ እራሳችንን ቅጥ ያጣ ውድቀት ከመጋፈጥና ተገቢውን ከማድረግ ይልቅ የሰበብ ድሪቶ እየደረትን ከእውነታው መሸሽ ክፉ ልማድ ሆኖብን ነው እንጅ ከሦስት ዓሥርተ ዓመታት በኋላም ተዘፍቀን የቀጠልንበት ግዙፉና መሪሩ እውነት ይኸው ነው። የትኛውንም ዲስኩር ምን ማለት ነው ? ለምን? እንዴት? ከየትስ ወደ የት? ብለን ሳንጠይቅ በግልብ ስሜት በታጀበ ጭብጨባና ጩኸት አሜን እያልን የመቀበላችን ክፉ ልማድ ምን ያህል እንደጎዳን ለማወቅና ለመማር  ከሦስት ዓመታት በላይ በመሬት ላይ ያለውን ግዙፍና መሪር እውነታ ወደ እራሱ  የቅዠት ዓለም ( his own illusional and delusional realm)  እየተረጎመና እያቀነባባረ “እውነት እውነት እላችኋለሁ እመኑኝ” በሚል ዲስኩሩ የሚታወቀውን ጠቅላይ ሚኒስትር ከምር ልብ ማለት ብቻ በቂ ነው።

በአንድ ወቅት   ተፎካካሪ ተብየ ፖለቲከኞችን ሰብስቦ “ለውጥ የሌለ የሚመስላችሁ በልጅነታችሁ ለመጀመሪያ ጊዜ መኪና ላይ ተሳፍራችሁ መኬናው ወደ ፊት ሲሽከረከር መሬቱና ዛፉ ወደ ኋላ የሚሄድ  እንደሚመስላችሁ ሆኖባችሁ ነው” በሚል ሲሳለቅባቸው ማጨብጨባቸውን ከምር ለታዘበ ሰው ከዚህ በታች የምጠቅሰው የቴዎድሮስ ካሳሁን ምናባዊ ንግግር (ዲስኩር) በስሜት ትኩሳት የታጀበ ጭብጨባና ጩኸት ቢቸረው የሚገርም አይደለም።

ቴዎድሮስ ካሳሁን ለዘመኑ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎች ምሥጋና ይግባውና በቦታው ለተገኙ ታዳሚዎች ብቻ ሳይሆን በእየ እጅ ስልኩ ላይ ይከታተለው ለነበረ ሁሉ ለተሰጠው አክብሮት ምላሽ በሰጠበት እጅግ አጭር ዲስኩሩ ውስጥ ዋነኛ ከሆኑ መልእክቶቹ  አንዱን “ላለፉት ቀላል ላልሆኑ ዓመታት አገራችን አስጨንቆ የያዛትና አሁንም ላለችበት ቀውስ የዳረጋት የጎሳ ፖለቲካና ሃሳብ እንደማነኛውም ሃሳብና ፍልስፍና ተወልዶ፣ አድጎ፣ አርጅቶና በስብሶ ተፈጥሯዊ ሞቱን ሞቷል” ሲል ይገልፀዋል።

ልክ ኢትዮጵያ ለዘመናት ከመጣችበት እና አሁንም የቀድሞ ጌቶቻቸውን ከቤተ መንግሥት አስወጥተው ጥርሳቸውን ነቅለው ያደጉበትን እኩይ የጎሳና የቋንቋ ማንነት ፖለቲካ ሥርዓት አስከፊ በሆነ የተረኝነት አገዛዝ ካስቀጠሉት ሸፍጠኛና ሴረኛ ግዥ ቡድኖች በአንዳች አይነት ተአምር (ምትሃት) የተላቀቀች እስኪመስል ድረስ ጭብጨባውና ጩኸቱ አስተጋባ።  አዎ!  የሚቀርብለትን ዲስኩር (ንግግር) ፍሬ ሃሳብና ተጠባቂ  ውጤት ሳይሆን የተናጋሪውን ማንነት ብቻ እያሰበ በየዓረፍተ ነገሩ ወይም በየአንቀፁ መጨረሻ ጭብጭባና ጩኸት በማስተጋባቱ እርካታ የሚሰማው ትውልድ የእራሱን እጣ ፈንታ በእራሱ የመተማመን መርህና ተግባር ላይ ተመሥርቶ  ለመወሰን በእጅጉ ይቸገራል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የወያኔ ምርጫ - ገረጭራጫ! (ሥርጉተ ሥላሴ)

መቸም የእራችንን ልክ የሌለው ድክመት ወይም ውድቀት ተጋፍጠን ተገቢውን እርምት የማድረጉ ወኔ ሲያጥረን የሰበብ ድሪቶ እየደረትን እራሳችንን መሸንገል (ማታለል) ክፉ ልማድ ካልሆነብን በስተቀር ለዓመታት በመማርና ማስተማር ሂደት ውስጥ አልፎ የመመረቂያ ገዋንና ቆብ ያጠለቀ ወጣት ትውልድ በመሬት ላይ ካለው ግዙፍና መሪር ሃቅ ጋር ጨርሶ የማይገናኝ ዲስኩር ሲደሰኮርለት በወቅቱ በስሜታዊነት ወይም በሌላ ምክንያት ለማጨብጨብና ለመጮህ ቢገደድም እንኳ ቆይቶም (አድሮና ውሎም) ቢሆን “የሰማሁትና ያጨበጨብኩለት የንግግር ይዘት እውን ግዙፉንና መሪሩን ሃቅ ይገልፃልን?” ብሎ እራሱን ለመጠየቅ የሚያስችል ወኔ አላገኘም።

ለዚህም ነው በመንበረ ሥልጣን ላይ የሚፈራረቁ ፈሪ፣ ባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች ሁሉ የኦሮሚያው ገዥ ሽመልስ አብዲሳ እንደነገረን ሲችሉ በርካሽ ፕሮፓጋንዳቸውና በፍርፋሪያቸው በማሳመን (convince) በማድረግ እና  ካልሆነ ደግሞ ግራ እያጋቡ (confuse) እያደረጉ ይህን ትውልድ ባለቤት እንደ ሌለው እንስሳ ወደፈለጉት አቅጣጫና ግብ የሚነዱት ።

አንዳንድ ወገኖች እንደ ቴዎድሮስ አይነት በሙያው የህዝብ እውቅና (popularity) ያገኘን ሰው ተሳስቷል ማለትን እንደ ክብረ ነክ ወይም እንደ ነውር በመቁጥር በሚመስል አኳኋን  ወይም እነርሱ እራሰቸው በሚያውቁት ሌላ ምክንያት  ግልፅና ግልፅ የሆነውን “የጎሳ ፖለቲካ አስተሳሰብና ፍልስፍና ተወልዶ፣አድጎ፣ አርጅቶና በስብሶ የመሞት” ምናባዊ ዲስኩር  ለማስተካከል እጅግ ሲቸገሩ መታዘብ ባይገርምም ምነው የፖለቲካ አስተሳሰባችን መርህ አልባ ሆነ? የሚል ጥያቄን ግን ያስነሳል።   የእውነተኛ መርህ ሰው የግለሰቦችን ዲስኩር የሚመዝነው ታዋቂ የሆኑ ወይም ያልሆኑ በሚል ሳይሆን የዲስኩራቸው (የንግግራቸው) ይዘት በመሬት ላይ ያለውን ግዙፍና መሪር እውነታ ያንፀባርቃልን? ወደ ተሻለ የተግባር እርምጃ ለመራመድ ያግዛልን?  የሚሉ ቁልፍ ጥያቄዎችን መመለስ ከመቻል ወይም ካለመቻል አንፃር ነው።

አዎ! ትክክል ያልሆነን ነገር ትክክል አይደለምና ይታረም ብሎ በአክብሮትና በገንቢነት ለመናገር (ለመግለፅ) የትምህርት ደረጃን፣ የማህበራዊ ግንኙነት ተቀባይነትን ፣የሙያ ታዋቂነትን ፣ የፖለቲካ ሥልጣን ደረጃን ፣ የእድሜ ባለፀጋነትን፣ የሃይማኖት መሪነትንና ሰባኪነትን ፣ በግል መተዋወቅን ፣ወዘተ መመዘኛ ማድረግ ፈፅሞ አይጠቅም። የሚጠይቅ መሆንም የለበትም። ከዚህ አይነት ኋላ የቀረና ደካማ የፖለቲካ አስተሳሰብ እራሳችንን በአንፃራዊነት ነፃ ሳናወጣ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ቁማርተኛ ገዥ ቡድኖችን አስወግደን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን ማለት ባዶ ምኞት ነው የሚሆነው። ለታዋቂነት የምንሰጠው ትርጉምና ዋጋም መመዘን ያለበት ከዚሁ መሠረታዊ ሃሳብ አንፃር መሆን ይኖርበታል።

በመሬት ላይ ካለው ግዙፍና መሪር እውነታ በተቃራኒ የጎሳ ፖለቲካ አስተሳሰብና ፍልስፍና “ተፈጥሯዊ ሞቱን ሞቷል” የሚልን እጅግ የተሳሳተና አሳሳች ዲስኩር ቢያንስ “ምነው እየተስተዋለ እንጅ” ለማለት ወኔው የሚሳነን ከሆነ እውነትም እየኖርን ያለነው በክፉ ቅዠት (illusion) ውስጥ እንጅ በእኛው በእራሳችን ገሃድ ዓለም  እውነታ ውስጥ  አይደለም ማለት ነው።

አገር በአንድ በኩል የአፈና እና የማጭበርበር ስልትን እያጣመሩ መንበረ ሥልጣኑን በተረኝነት በተቆጣጠሩ የጎሳ/የቋንቋ  አጥንት ስሌት ፖለቲካ ቁማርተኛ ገዥ ቡድኖች እና በሌላ በኩል ደግሞ ሁሉን አድራጊነታችን ተደፈረብን በሚሉ የአንድ ሥርዓት ( የኢህአዴግ ሥርዓት) ሁለት አንጃዎች ወይም ጁንታዎች  መካከል በሚደረግ እጅግ አሳፋሪና አሰቃቂ የሥልጣን ሽሚያ ጦርነት ምስቅልቅሏ እየወጣ  ባለበት መሪር እውነታ ውስጥ የጎሳ ፖለቲካ አስተሳሰብና ፍልስፍና እንደ በሰበሰና እንደሞተ አድርጎ መደስኮር ለተሰጠን ወይም ለሚሰጠን የታዋቂነት እውቅና ጨርሶ አይመጥንምና ከምር ልብ ልንለው ይገባል።

ታዋቂነት ማለት ሁሉን ማወቅ እና ከሂሳዊ ትችት ነፃ መሆን ማለት አለመሆኑን ባንወደውም በመቀበል ለእርምት ዝግጁዎች መሆን ይኖርብናል። ከዚህ በተቃራኒ ያለው አስተሳሰብና ባህሪ የውድቀት እንጅ የስኬት ምክንያት  አለመሆኑን ለአያሌ ዓመታት አይተነዋልና ጨርሶ ልናስወግደው ባንችል ከምር ልናርመው ይገባናል።

ይህን ለማድረግ ዝግጁዎች እንደምንሆንና  እንደምንችልም ያለኝን ተስፋ እየገለፅሁ አበቃሁ።

6 Comments

  1. አረ ጌታዬ ሰብሰብ በሉ ጽሁፎ ለትችት እንደሚያጋልጦት እርሶም ስለተረዱት ፈራ ተባ እያሉ የነገሬን ጭብጥ ተረዱት አይነት ነገር አስፍረዋል። እርሶስ በቴዲ ልኬት ደረጃዎ ምን ይሆን? ቴዲን እንዲህ ጥምብ እርኩሱን ያወጣው የርእዮት ሚዲያ ባለቤት ቴዎድሮስ ጸጋዬ ነው. እርሱ ላይ አልፈርድም ኢትዮጵያዊነት ላይ ባለው ጥላቻ። በተረፈ ይህን ያህል ያልተመጣጠነ ትችት ያነሱበት ቂም ቋጥረውበት ካልሆነ ትችቶ አመንክዮ የለውም።

  2. Arnet, let me first say thank you for expressing your idea in any way you understand it.
    But can you tell me or teach me in what way or in what sense I either misquoted or misunderstood him? Are you saying that the words of his own I carefully quoted need kind of highly sophisticated literature of gold and wax or msitre-kine or an extraordinary philosophical interpretation?
    I sincerely appreciate and respect one’s courage to express his or her own ideas and views. But I equally believe that there must be some sort reasoning or substantiation whenever we try to challenge any idea we want to challenge.
    Simply saying that somebody is wrong or right is not an argument in a real sense of the term at all. That is why I am asking you to answer the question: what did Tewodros want to say when he said the words I carefully quoted? What he tried to say when he strongly declared or announced that “the very politics of ethnicity has died its natural death”. That is simple and clear! Words have their own meaning. If we want to be clear to our listeners, we need to pay due attention what we want to say and how we want to say it. Try hard to defend the indefensible by bringing in all kinds of excuses that are irrelevant to the very subject matter if making things worse. If you are really a sincere admirer of Tewodros , tell him that he wrong !
    Thanks sir or madam!

  3. Tegenaw Goshu wrote an article to condemn, criticize and damage the reputation of Teddy Afro in his short speech made at Gondar University. As usual, the deep-seated despise and hatred of this person who is suffering from narcissistic personality disorder is trying to paint Teddy Afro in the wrong way. Arnet and Berelea were respectfully commenting to this vile person that he was dead wrong when he tries to meddle with the untouchable Ethiopian heroes. As for my approach, I would rather call it a spade a spade, because I saw this type of arrogant sick with a lack of empathy and respect for the majority of Ethiopian’s repeatedly. I would share this.
    Tegenaw Goshu may not be a real person, but a TPLF sympathizer with Amhara’s name and he is the number one Junta supporter and he is doing everything possible in his power to defend Woyane and other anti-Ethiopia elements at any cost. He is fighting hard tooth and nail to defame Ethiopia and everything Ethiopians stand for as he is one of TPLF undercover operating here in Ethiopian electronic media to spew his hateful agenda against Ethiopians. His approach is the carbon copy of Woyane’s blueprint that hates anything Ethiopian. Tewodros Kassahun and Abiy Ahmed are the two most beloved sons of Ethiopia. For Woyane and their operatives like Tegenaw Goshu and Tewodros Tsegaye of Reeyot who hates to their core the adored and admired Ethiopians are the whole mark of Tigray People Liberation Front (TPLF). Tegenaw was happily serving TPLF when Teddy Afro pays an enormous sacrifice when jailed for years in cooked and trumped-up charges by TPLF because his national unity and integrity songs were against their agenda. Teddy Afro contributes the lion’s share of his musical talent to Ethiopia’s integrity, love, unity, and sovereignty than this venomous and shrewd hater of anything Ethiopian narcissist. He has no moral authority to utter a word about or against Teddy Afro’s assertion. Yes, tribalism and ethnicity are decayed and buried and this truth is entertained, believed, and reflected by most Ethiopians except by a few fringe elements like Tegenaw, Tewodros Tsegaye, and Woyane sympathizers. I would like to ask readers of this comment, just ask yourself as to why this sick individual who always hates anything Ethiopian and is loved by Ethiopians write such venomous attacks every time? The mind-boggling question to this delusional person is why on earth, Tegenaw (Hagos) is upset to such a degree and be antagonistic and spews his vile hatred to the most admired Ethiopian Icons?

  4. Liji Ejgu,
    I sincerely would like to say that it is absolutely up to you to have your own say about anything in any way you understand it and believe in it. That is the way we practice what a democratic culture of conversation is all about. So, do not get terribly upset and try to turn things up side down unnecessarily because it is a very backward and infantile political mentality and moral degradation which make us victims of failure for so many years and still languishing in.a much more worse manner.
    You and I have very different understanding and views as far as the very hard political reality of our country is concerned . But I sincerely want to argue that we have no either any personal acquaintance or enmity at all . Unfortunately, the way your said sounds like we personally hate and attack each other . Alas! all what you wanted to say has nothing to do with responding or challenging my central point about the very speech of Tewodros Massaun . Why did not you try to invalid my main point by having your own substantiated and convincing reasoning instead of just throwing all kinds of personal insults that do not make sense to any reasonable person leave alone to me . I have to tell you that what worries me is not what you tried to say about me , but the very backward and extremely infantile political mentality and culture we could not get rid off and move forward accordingly .
    I do not think the way you tried to portrait the prime minister of cynicism , hypocrisy, conspiracy , dishonest, narcissism, infantility (childish) , lack of sincere empathy , extremely misleading, and of course ruthlessness does not reflect the vey hard reality the Ethiopian people are suffering from.
    It is terribly wrong to portrait him as a great son of Ethiopia whereas the country has gone down to an extreme miserable direction . I hate to but I have to tell you that the country will never get better leave alone to be a country of democracy with the leadership of this guy who grew up in the very cancerous political realm of TPLF/EPRDF and has keep going with the same deadly political system of ethnocentrism.
    With regard to Tewodros Kassagun, I did not undermine what he has contributed in the field of art (music) .But I strongly argued that his declaration or slogan about the total demise of the politics of ethnicity is very shallow and foolishly misleading !

  5. Nothing has been changed and I will never expect this sickness and narcissistic behavior of Tegenaw and all TPLF juntas and their sympathizers will go away easily. Let me explain what a narcissistic personality looks like by quoting the following.
    “You will go from being the perfect love of their life to nothing you do is ever good enough. You will give everything and they will take it all and give you less and less in return. You will end up depleted. Emotionally, mentally, spiritually, and probably financially, and then get blamed for it.” This was exactly what Tegenaw and TPLF are doing as they are being eaten alive by their own creation of deep hatred, extreme disgust, and resentment against Ethiopia and Ethiopians. As most of you know, Professor Almariam was fighting TPLF with his sharp pen for the last 14 years, and look what Tegenaw, an ardent TPLF supporter wrote back in July 2019 against this highly respected Ethiopian scholar. https://amharic.zehabesha.com/is-it-not-fallacious/ Now, most Ethiopians have admired those two heroes of Ethiopia namely, Dr. Tewodros Kassahun and Dr. Abiy Ahmed are giving everything they have. Yet, Tegenaw and TPLF are taking all and gives back zilch to the hands that fed them. The Ethiopian people were embezzled left and right by TPLF and the likes of Tegenaw. Because of their deep-rooted hatred of Ethiopia, they started their war from Mekele to destabilize the country and 112 skirmishes have been orchestrated by the Junta and the blind supporters of TPLF. Ethiopia suffered from untold misery and bloodletting. They came back from the back door and start blaming Abiy Ahmed and Teowdros Kassahun for their own sin. Most Ethiopians acknowledged that this war was started by TPLF when they attack the northern command and also knows what the PM was doing to avert this catastrophe. But see what Tegenaw the TPLF spokesperson wrote back in November 2020. https://amharic.zehabesha.com/what-is-really-the-very-end-result-of-this-very-devastating-war/ Tegenaw and TPLF came back again to blame the prime minister of Ethiopia in collaboration with the western entities that their interest is to dismantle that historic country to many small fragile regions. TPLF and Tegenaw (Hagos) are working to accomplish this. No matter how hard you try Tegenaw or TPLF, we know who you are and let me tell you this, there will not be any gullible Ethiopian anymore to be distracted by your poisonous propaganda that helps to reinstate those traitors and bandits in the disguise of public discourse while we know you are spewing poison to change hearts and minds of some by your fake stories. But trust me, there will not be any Ethiopian that will be fooled by your propaganda, and there is no one Ethiopian in this difficult time to throw mud on PM Abiy and Teowdros Kassahun and most of all to our military forces unless he or she is a TPLF member that is fighting tooth and nail to reclaim victory of spreading their hatred to a few who could lend them an ear as they are losing big time on the battleground. Tegenaw is a TPLF member with Amhara’s name who propagates his deep-rooted hatred to Ethiopia and anything Ethiopian. Anyone who is interested to know about this wolf on ships cloth, just type his name on google and read what kind of hateful propaganda he wrote against Ethiopia and our common values, and all of his views are distorted and woefully serving the enemies of our country. He has a very twisted outlook full of ego that he thinks he is the only savior of TPLF by being antagonistic to Ethiopian icons. If he is interested in civil discourse and if he is not a TPLF member disguised in the Amhara name, let him put his email address on his articles like many Ethiopian writers and I will be willing to discuss with him and remove his cloaks.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share