እጅግ ተጎሳቁለዋል!!!
ከአንድ ወር በፊት ከቤታቸው በሌሊት ተወስደውና አድራሻቸው ጠፍቶ የቆዬው ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ በአሁኑ ሰዓት ገላን ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ታስረው የሚገኙ ሲሆን እስካሁኗ ስዓት ድረስ ፍርድ ቤት አልቀረቡም። ከተያዙበት ዕለት ጀምረው ወደ አዋሽ መልካ ተወስደው ለ22 ቀናት በጨለማ ቤት ታሰረው በቀን አንድ ጊዜ ብቻ ምግብ እየቀረበላቸው ከቆዩ በኋላ አሁን ወደሚገኙበት ጣቢያ ተዛውረው ታስረው ይገኛሉ።
በፖሊስ መምሪያው ምንም ዓይነት ምግብ የማይቀርብላቸው ሲሆን በራሳቸው ገንዘብ በፖሊሶች መልካም ትብብር እየገዙላቸው ህይወታቸውን እስካሁን አቆይተዋል። እጅግም ተጎሳቁለዋል።
አሁን በአካልን ነፃ ማውጣት ህግ ከእስር እንዲለቀቁ ሁላችንም የምንችለውን በማድረግ ልንረዳቸው ይገባል።
የደረሰባቸውን እንግልት ወደፊት ከእራሳቸው አንደበት እንሰማዋለን።
በለጠ ጌትነት
እነ ታየ ደንዳ እነ ሐጎሶች ቁጭ ብለው እኝህ ድንቅ ኢትዮጵያዊ ሲታሰሩ ምን እየተሰራ ነው ያስብላል። እውን አቶ ታዲዮስ ከአባ ዱላ ክአርከበ ከሳሞራ በላይ ይህችን አገር በድለው ነው?ፍርዱን አምላክ ይስጥ
በአንጋፋው የታሪክ ሠው ታዲዮስ ታንቱ ላይ የተደረገው አፈና ዛሬም ፍትህ ነጻ አለመውጣቱንና እውነትን መናገር ዋጋ ተሚያስከፍል መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።
ፍትህ ለንጹሃን አሁኑ!!!