July 6, 2021
2 mins read

የማይካድራው ጨፍጫፊ ቡድን ሳምሪ በሱዳን የስደተኞች ካምፕ ውስጥ እንዳለ አሸባሪው ሕወሃት አስታወ

አማራ ሚዲያ ማዕከል

ሰኔ 29/2013 ዓ.ም በሕግ ማስከበር እርምጃው ከሚጠብቀው በተቃራኒ ነገሮች በፍጥነት የተቀየሩበት አሸባሪው ሕወሃት ሽንፈቱን በአማራ ሕዝብ ላይ ባነጣጠረ ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ደመደመ፡፡
214842969 5672003109540929 2564695600804994807 n 1
በማይካድራ የሚገኙ ንጹሃንን ጨፍጭፈው ወደሱዳን የሸሹት ቡድኖች የራሱ ወታደሮች መሆናቸውን አሸባሪው ህወሓት ዘግይቶም ቢሆን አስታውቋል፡፡
አሸባሪው ህወሓት ያደራጃቸው እና በአማራ ላይ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ ያካሄዱት ሳምሪ የተባሉት ወጣቶችና ሚሊሻዎች በሱዳን በስደተኛነት ስም ተጠልለው እንደሚገኙ ታውቋል፡፡
ጉዳዩ ቢዘገይም አሸባሪው ህወሃት እነዚያ ገዳይ ቡድኖች በሱዳን እንደሚገኙ ተናግሯል፡፡ አሸባሪው ቡድን ለፋይናንሻል ታይምስ እንደገለጸው እስከ 30 ሺህ የሚጠጋ ወታደር በሱዳን አለኝ ብሏል።
ፋይናንሻል ታይምስ የአሸባሪው ቡድን አመራሮች ነገሩኝ እንዳለው ለጦርነት ዝግጁ የሆኑ 30 ሺህ ወታደሮች በሱዳን ተጠልለው አሉ ብሏል፡፡
ሳምሪ በሚል መጠሪያ አሸባሪው ቡድን አደራጅቷቸው የነበሩት ገዳዮች በማይካድራ ቤት ለቤት በመዞር መታወቂያ እየተመለከቱ አማራዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ መጨፍጨፋቸው ይታወሳል።
መንግሥት በተደጋጋሚ የሳምሪ አባላት በሱዳን የስደተኞች ካምፕ በስደተኛ ሥም እንደተጠለሉ ሲገልጽ ቢቆይም ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብም ሆነ የብዙኀን መገናኛ ተቋማት ጉዳዩን መስማት የፈለጉ አይመስሉም ነበር፡፡
ዘግይቶም ቢሆን ግን አለማቀፉ ማኅበረሰብ መስማት ያልፈለገውን እውነት ህወሃት የመንግሥት ተደጋጋሚ ጩኽት ትክክል እንደነበር ይፋ አድርጓል፡፡
አሚኮ እንደዘገበው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Atalayar Pruebas Detección Coronavirus Emiratos Árabes Unidos Dubái 6
Previous Story

አይ ሀገሬ ኢትዮጵያ! ሰውን ለማዳን የማለው ሰውን ጨረሰው (እልማዝ አሰፋ-ዘረ ሰው)

Next Story

በጣር የታጀበ አደራ – መኮንን ብሩ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop