July 6, 2021
2 mins read

የማይካድራው ጨፍጫፊ ቡድን ሳምሪ በሱዳን የስደተኞች ካምፕ ውስጥ እንዳለ አሸባሪው ሕወሃት አስታወ

214842969 5672003109540929 2564695600804994807 n 1

አማራ ሚዲያ ማዕከል

ሰኔ 29/2013 ዓ.ም በሕግ ማስከበር እርምጃው ከሚጠብቀው በተቃራኒ ነገሮች በፍጥነት የተቀየሩበት አሸባሪው ሕወሃት ሽንፈቱን በአማራ ሕዝብ ላይ ባነጣጠረ ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ደመደመ፡፡
214842969 5672003109540929 2564695600804994807 n 1
በማይካድራ የሚገኙ ንጹሃንን ጨፍጭፈው ወደሱዳን የሸሹት ቡድኖች የራሱ ወታደሮች መሆናቸውን አሸባሪው ህወሓት ዘግይቶም ቢሆን አስታውቋል፡፡
አሸባሪው ህወሓት ያደራጃቸው እና በአማራ ላይ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ ያካሄዱት ሳምሪ የተባሉት ወጣቶችና ሚሊሻዎች በሱዳን በስደተኛነት ስም ተጠልለው እንደሚገኙ ታውቋል፡፡
ጉዳዩ ቢዘገይም አሸባሪው ህወሃት እነዚያ ገዳይ ቡድኖች በሱዳን እንደሚገኙ ተናግሯል፡፡ አሸባሪው ቡድን ለፋይናንሻል ታይምስ እንደገለጸው እስከ 30 ሺህ የሚጠጋ ወታደር በሱዳን አለኝ ብሏል።
ፋይናንሻል ታይምስ የአሸባሪው ቡድን አመራሮች ነገሩኝ እንዳለው ለጦርነት ዝግጁ የሆኑ 30 ሺህ ወታደሮች በሱዳን ተጠልለው አሉ ብሏል፡፡
ሳምሪ በሚል መጠሪያ አሸባሪው ቡድን አደራጅቷቸው የነበሩት ገዳዮች በማይካድራ ቤት ለቤት በመዞር መታወቂያ እየተመለከቱ አማራዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ መጨፍጨፋቸው ይታወሳል።
መንግሥት በተደጋጋሚ የሳምሪ አባላት በሱዳን የስደተኞች ካምፕ በስደተኛ ሥም እንደተጠለሉ ሲገልጽ ቢቆይም ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብም ሆነ የብዙኀን መገናኛ ተቋማት ጉዳዩን መስማት የፈለጉ አይመስሉም ነበር፡፡
ዘግይቶም ቢሆን ግን አለማቀፉ ማኅበረሰብ መስማት ያልፈለገውን እውነት ህወሃት የመንግሥት ተደጋጋሚ ጩኽት ትክክል እንደነበር ይፋ አድርጓል፡፡
አሚኮ እንደዘገበው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Atalayar Pruebas Detección Coronavirus Emiratos Árabes Unidos Dubái 6
Previous Story

አይ ሀገሬ ኢትዮጵያ! ሰውን ለማዳን የማለው ሰውን ጨረሰው (እልማዝ አሰፋ-ዘረ ሰው)

Next Story

በጣር የታጀበ አደራ – መኮንን ብሩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop