“አይ AM NASTY?!!” በሐገር ቤት ስላሉ የሰብዓዊ መብቶች ነጋዴዎች እና ስለ ፍስሐ ተክሌ

ከታዛቢ – የካቲት 19 / 2013 ዓ.ም.

ይህን አጭር ጽሁፍ እንድጽፍ ያስገደደኝ (ያበረታታኝ?) ደጀኔ አሰፋ ነው፤ አምነስቲ ኢንተርናሽናል – “አይ AM NASTY?!!” አለው ደጀኔ!? – ዛሬ ያወጣው መግለጫም ለዚህ ጽሁፍ የራሱ አስተዋጽዖ አለው፡፡ ደጀኔ አሰፋ፣ ስለ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የምሥራቅ አፍሪካ ቅርንጫፍ (Hub)፣ በተለይም ስለ ፍስሐ ተክሌና ሐበን ፈቃዱ፣ በዘሐበሻ ፌስ ቡክ ገጽ ላይ ዛሬ ያጋለጠው መረጃ በራሱ ዓይን ገላጭ ነው፡፡ የደጀኔ ማስረጃ የሚያሳየው የራያን አውድ ብቻ ቢሆንም፣ ዕውነት እንደሚሆን ግን እኔ ጥርጥር የለኝም፡፡ ምክንያቱም የርሱን ቅሬታና ማስረጃ የሚያረጋግጡ በሌሎች አውዶች ሊቀርቡ የሚችሉ በጣም ብዙ ማስረጃዎች ስላሉ ነው፡፡ ስለ ሐበን ፍቃዱም የገለጸው ትክክል ነው፤ የፍስሐ ተክሌ ተባባሪ ስለመሆኗ ማስረጃ አለ (አንዳንዴ የሚጣሉ ቢመስሉም)፡፡

ዓለም አቀፍ ሸረሪት እና ሰብዓዊ መብቶች ነጋዴዎች

ደጀኔ የገለጸው እነፍስሐ ከወያኔ ጋር የነበራቸውንና ያላቸውን የጥቅም ግንኙነት ብቻ ነው፡፡ መረባቸው ግን ተቋም-ተሻጋሪ፣ ብዙ ሰው ሊገምት ከሚችለው በላይ የሰፋ፣ የተወሳሰበና አስፈሪም ነው፡፡ ሥሩን ባሕር ማዶ ያደረገና ሐገር ቤትም ሰፊ መረብ/ቅርንጫፍ ያለው ዓለም አቀፍ ሸረሪት አለ፡፡ እነ ፍስሐ ተክሌ በውጭ የሚገኙ የሸረሪቱ ድሮች ናቸው፡፡ ከለውጡ በፊትም ዛሬም በሐገር ቤት ተንሰራፍተው የሚገኙ የዚሁ ዓለም አቀፍ ሸረሪት / ኔት ዎርክ አካል የሆኑ የሰብዓዊ መብቶች ነጋዴዎች (Human Rights Entrepreneurs) አሉ፡፡ እነዚህ በሐቀኛ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅት እና በሰብዓዊ መብት ልዩ ልዩ ስሞች በሚንቀሳቀሱ “የቦርሳ ውስጥ ድርጅቶች” ውስጥ በአመራርነት ተሸጉጠውና ራቅ ብለውም በአማካሪነት ስም መሽገው ይገኛሉ፤ በሰብዓዊ መብቶች ታጋይነት ስም የግል ጥቅማቸውን ሲያሳድዱ እስካሁን የቆዩ ናቸው፡፡ …

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለትግራይ ሕዝብ የዝማታ መነሻው “ፍራቻ” ከሆነ ከራሱ ሌላ የተሻለ ነፃ አውጪ ከየት ይመጣል? (ጌታቸው ረዳ)

ፍስሐ ተክሌ በብሔሩ ከነዚህ ቢለይም የነዚህ ነጋዴዎች የቅርብ ጓደኛና የጥቅም ተባባሪ ነው፤ (ከሰብዓዊ መብቶች ነጋዴዎቹ የሐገር ውስጥ መረብ አመራሮችና አባላት መካከል የሚበዙት የአማራ ተወላጆች ናቸው)፡፡

የሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት ፋብሪካዎች (Human Rights Project Factories)

እነዚህ የሰብአዊ መብቶች ነጋዴዎች “የተማሩ” ናቸው፤ “የታወቁ” የሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክቶች ፋብሪካዎችም ናቸው፡፡ መሬት ላይ የማይወርዱ፣ ለሕዝብና ለሐገር የረባ ጥቅምና ለውጥ የማያመጡ ልፍስፍስ ፕሮጀክቶችን ቀርጸው ይቸበችባሉ፡፡ ለነዚህ ፕሮጀክቶቻቸው ማስኬጃ የሚያስፈልጋቸውን ገንዘብ በዶላርና በዩሮ የሚሰጧቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት አሉ፡፡ ዋናዋናዎቹም የፋብሪካው መሥራችና መሪዎችም፣ ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ ለሆነ አንዳንድ ኤምባሲዎች “የአማካሪነት” አገልግሎት ይሰጣሉ፡፡

ሐገር ቤት ላሉት የሰብዓዊ መብቶች ነጋዴዎች የገንዘብ ድጋፉን የሚያሳልጡላቸው፣ ፍስሐ ተክሌን የመሰሉ፣ በልዩ ልዩ ዓለም አቀፍ “የነጻነት፣ የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብቶች” ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ የጥቅም ተካፋዮቻቸው ዛሬም አሉ፡፡ አንዳንዴ በኤክስፐርትና በተንታኝ ስም በዓለም አቀፍ ሜዲያዎችና መድረኮች ላይ አፍቃሪ ወያኔና ጸረ ኢትዮጵያ ዘመቻ ሲያካሂዱ እያየናቸው ነው፡፡ የሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክቶች ፋብሪካ የሆኑት የሰብዓዊ መብቶች ነጋዴዎች በነፍስሐ ተክሌ አማካኝነት እና ራሳቸውም ባላቸው ግንኙነት ከሚያገኙት ዶላርና ዩሮ ውስጥ 80 በመቶው ራሳቸው ኪስ የሚገባ ነው፡፡ አንዳንዴም በፕሮጀክት ድግግሞሽና ተመሣሣይነት ምክንያት የእርዳታ ሰጪውን ቅድሚያ ለማግኘት እርስ በርስ ሲሻኮቱ ታገኛቸዋለህ፡፡ ክፋቱ ወዲያው መልሰው ይገጥማሉ!

ሸረሪቷና ድሯ የሚናቁ አይደሉም!

የነፍስሐ ተክሌንና በውስጥ ያሉትን ነጋዴዎች ሥፍር ቁጥር የሌለው ጉድ ልታጋልጥ ብትሞክር የሚሰማህ የለም/አልነበረምም፡፡ ችግሩ የወያኔ ሽፋን ሰጪነትና የኔት ዎርኩ ጠንካራና ሰፊ መሆን ብቻ አይደለም፤ ነጋዴዎቹ ትርፍራፊ የሚጥሉለት፣ ተስፋ የሚሰጡት፣ አድርባዩ፣ ፈሪውና ነገሩ ያልገባው ሁላ ያዋክብሃል ወይም ቸል ይልሃል! ከነጋዴዎቹ ጋር ብትተቃቀፍ ደግሞ የሚያቀርቡልህ ቁሳዊ ጥቅም የሚያማልል ነው፤ ጥቅሙን በነርሱ ኑሮና አኗኗር ላይ ታየዋለህ፡፡ የሰብዓዊ መብቶች ነጋዴዎቹን እና አምነስቲን ጨምሮ ዓለም አቀፍ መረቡን ለመጋፋት መሞከር አደገኛ ነው፡፡ በነጋዴዎቹ በራሳቸው፣ በሥውር እጆችና በእጀ ረዥሞቹ የሚከፈትብህ ዘመቻና የሚያርፍብህ ጥቃት መዘዙም ብዙ ነው፡፡ የሚሰማቸው የዋህና እነርሱን መሰል መሰሪም ያገኙ ከመሰላቸው የወያኔ ቅጥረኛ እንደሆንክ አድርገው ሁሉ ስምህን ያጠፉታል፡፡ ዛሬ ሌላ ቀን ቢሆንም፣ “እንኳን ዛሬ፣ እንኳን እናንተን፣ ትናንትም ወያኔን ራሱን አልፈራንም!” ብትልም አይበቃም፡፡ ፍስሐ ተክሌንም ሆነ የሐገር ቤቶቹን የሰብዓዊ መብቶች ነጋዴዎች እንደ ግለሰቦች ብቻ መመልከት ስህተት ነው! እነርሱ ተቋም፣ ሰፊና ውስብስብ መረብ እንዲሁም መቀመጫዋን ውጭ ያደረገች የትልቅ ሸረሪት ድሮች ናቸው!! ከነርሱ ጋር የሚደረገውም ትግል ከፍተኛ ብልሐትና ጥንቃቄን ይጠይቃል!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ያማራ ሕዝብ የዘር ማጥፋትና ማጽዳት፣ ከመናገሻ አዲስ አበባ የማስወጣቱ ዘመቻ!

የኢትዮጵያ ዋርካና የሰብዓዊ መብቶች አባት፣ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም ከማለፋቸው ከወር በፊት፣ እነዚህን የሰብዓዊ መብቶች ነጋዴዎች፣ “ጋዜጠኞች/ ሜዲያ ጠርቼ በአደባባይ ለሕዝብ አጋልጣቸዋለሁ!” ብለው ነበር፡፡ ይህን ማለታቸውን ማረጋገጥ የሚፈልግ፣ በህልፈታቸው ማግሥት በኢሳት ቴሌቪዥን ላይ በዓይን እማኝ መገለጡን ማጣራት ይችላል፡፡ ሞት ቀደማቸው!

አሁን ለሐገርና ለሕዝብ ሕልውና ሲባል፣ ለመነጋገር ጊዜው ግድ የሚልና የደረሰ ይመስላል! ይህ ለሕዝብና ለሚመለከተው ክፍል ፍንጭ እንዲሆን ብቻ ነው! ዝርዝሩማ ገና ምኑ ተነክቶ …

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ከአድፋጭ ሠይጣኖችም ይጠብቅልን!

 

 

1 Comment

  1. Dear Tazabi,
    It is the right thing to see the reports reported by various national and international organizations in a critical way as it is needless to say that they may not or cannot be as balanced and accurate as they should be . Not only the problem of being mistakenly skewed but also because of their own interior motives , seeing them critically is quite fair and necessary.
    However, trying to undermine what they did or are doing or will be doing for the simple reason you mentioned is a very simplified and wrong way of seeing things. The very terrible thing what TPLF did and now what its advocates are doing , and the problem or shortcoming reflected in Amnesty International report cannot and should not be excuses either to undermine or deny the very huge and bitter reality that has happened and continued to happen in the country .It is the right thing to rationally or objectively challenge the role of a person who involved in preparing and releasing the report . But it is totally nonsensical to try to either undermine or dismiss the report because that person belongs to this or that ethnic group or has some kind of bias toward this or that group. Whatever the case, those hypocritical and conspiratorial and extremely dishonest politicians of OPDO /EPRDF/Prosperity including the prime minister whose political personality is mainly characterized by the very ugly politics of narcissist , infantility, extremely misleading, and self-contradictory ( rhetoric vs reality) cannot and must not be allowed to escape the very responsibility and accountability for what happened and continued to happen in the country!!! Never and Never and Never ! Trying to use the very bad guys of TPLF as excuses for what the incumbent ruling circle which is not willing to stop what is happening in Oromia and Benisghagul-Gumuz of which OPDO/OLF forces are parts and parcels but decrying what TPLF and its advocates are doing is a very disingenuous and idiotic political way of thinking!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share