ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንቷ ምን ነካቸው? |ሕብር ራዲዮ ዜና ትንታኔ
ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንቷ ምን ነካቸው? |ሕብር ራዲዮ ዜና ትንታኔ
የእንግዳ ልኡክ ጽሁፎችን የአርትዖት አምዶችን ወይም አስተያየቶችን እና ትንታኔዎች መጣጥፎችን እንቀበላለን:: ሀሳበወትን እና እውቀትዎን ለአንባቢዎቻችን እንዲያካፍሉ እንጋብዛችኋለን። ጽሑፋችሁ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎችን ይደርሳል፣ ያለቀ ጽሁፍ በ admin@zehabesha.com በኩል ያቅርቡ! የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ደራሲውን ብቻ የሚያንፀባርቁ እንጂ የዘ-ሐበሻ ዶት ኮም ኦፊሴላዊ ፖሊሲ ወይም አቋም የሚያንፀባርቁ አይሆኑም!!
እኝህ ፈገግታ፤በቄንጥ መናገር፤መራመድ፤መቀመጥና ጥሩ መልበስ ግባቸዉ ያደረጉ የዶር አብይ ተሿሚ የፍርድ ተቋሙን እንዲመሩ የተሰየሙት ሴት ከተለያየ ቃለ መጠይቃቸዉና እሳቸዉ በተራቸዉ ከሚሾሟዋቸዉ ተሿሚዎች የምንሰማዉና የሚፈጸመዉ ድርጊት አስደንጋጭ ነዉ።
ሴትዮዋ የፍርድ ወምበር ላይ ቁጭ ከሚሉ ሊሆኑ የሚመኙትን የሞዴል፤የፊልም ስራ ኪነት ወይም ቱሪዝም ዉስጥ ቢመደቡ የተሻለ ስራ የሚሰሩ ይመስለኛል። ፍትህ ባናቱ ሂዶ እያዩ ፍርድ ቤት የለቀቀዉን ፖሊስ እየመለሰ በመላ ሀገሩ ሰብአዊ መብት ቀርቶ የመኖር መብት ባልተከበረበት አገር እንዲህ ከባጥ በላይ መንጠራራት ለሳቸዉም ጥሩ አይሆንም። የፖለቲካዉ ስራዉን ትተዉ ወደ ፍትህ ሀሳባቸዉን ቢያዞሩ መልካም ይመስለናል ከሆነላቸዉ።