February 25, 2020
2 mins read

63 የሚሆኑ ግለሰቦች ክስ መቋረጥን አስመልክቶ የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ -ሕግ አስታወቀ

Fed ethiopian registrar

ለሀገራዊ አንድነትና ለውጥ ሲባል በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ተጠርጥረው የነበሩና ጉዳያቸው በህግ ተይዞ የነበሩ የ63 ተጠርጣሪ ግለሰቦች ክስ እንዲቋረጥ መደረጉን ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ።

የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ቱኑ ጉዳዩን አስመልክቶ ዛሬ ከሰዐት በኋላ በሰጡት መግለጫ በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ተሳትፎ የነበራቸው ነገር ግን የአመራርነት ቦታ ያልነበራቸው ግለሰቦች ክስ እንዲቋረጥ ተደርጓል።

የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ሲባል ለጠቅላይ አቃቤ ህግ በተሰጠ ሀላፊነት መሠረት የ63 ሰዎች ክስ የተቋረጠ ሲሆን ተጠርጣሪዎች ደግመው ወደ ድርጊቱ የሚገቡ ከሆነ ግን አቃቤ ህግ ጉዳዩን ዳግም የማየት ስልጣን እንዳለው በመግለጫው ተጠቅሷል።

በዚህ አጋጣሚ ህግ የማስከበሩ ስራ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተገልጿል።

ክሳቸው የተቋረጠላቸው 63 ግለሰቦችን ዝርዝር ከደቂቃዎች በኋላ ይፋ እንደሚያደርግም ጠቅላይ አቃቤ ህግ በመግለጫው ጠቅሷል።

ድልነሳ ምንውየለት

ዛሬ ክሳቸው ከተቋረጠው 63 ግለሰቦች መካከል:

1. አቶ ኤርሚያስ አመልጋ
2. ኮ/ል ቢኒያም ተወልደ
3. አቶ ክርስትያን ታደለ
4. ረ/ፕሮፌሰር ተሰማ ኤልያስ
5. አቶ ሳሙኤል በላይነህ
6. አቶ አዲስ ቃሚሶ እና
7. አቶ አለም ፍጹም ይገኙበታል

Via Sheger Times
በሀሰት ተወንጅለው የተከሰሱትን ለመፍታት በሚል የአገር ሀብት የዘረፉ ትላንትም ስልጣንን ተገን አድርገው ወንጀል ሲሰሩ የነበቱትን መፍታት አግባብ ነው የሚል ጥያቄ እየተነሳ ነው። የእርስዎ አስተያየት ምንድነው!?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

addis ababa realethiopia 141
Previous Story

አዲስ አበባ ከምጧ “ፍቅርና ኢትዮጵያ” የተባሉ መንታ ልጆችን ተገላገለች፤ – ሰማነህ ጀመረ፤ ካናዳ

Next Story

የአባይ ግድብ የፖለቲካ ቁማር ወይስ ድርድር? – ሰርፀ ደስታ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop