September 8, 2024
7 mins read

አማራ መታገል ያለበት ለመኖር ብቻ ሳይሆን ታሪኩ እየተገሸለጠ እንዳይጣል፣ መቀበሪያ እንዳያጣና የተቀበረውም በግኒደር እየታፈሰ መወርወሩ እንዲቆም ነው!

የለም እስቲባል ድረስ አማራ ራሱን እረስቶ ስለኖረ ዛሬ የህልውና አደጋ ብቻ ሳይሆን መቀበርያ እያጣና የተቀበረውም በግንዲር እየተዛቀ ሲጣል ይውላል፡፡ በቋንቋና በዘራቸው ተደራጅተው ቋንጃህን ስልንስብር መጣን ሲሉትም  ምሁር ተብዬው “ለኢትዮጵያ ስንል፣ እንደነሱ አናንስም፣ ወዘተርፈ” የሚሉ ድስኩሮችና ሰበቦች እየደረደረ አማራ ተደራጅቶ ራሱን ስላልተከላከለ ዛሬ ላለበት የመከራ ዘመን እንደ ደረሰ ይታወቃል፡፡ ከዚህ የመከራ ዘመን አማራ ትልቅ ዘላለማዊ ትምህርት መቅሰም ሲኖርበት አንዳንዱ ከንቱ አንሁም እርስ በርሱ መናከሱንና መንዘላዘሉን ቀጥሏል፡፡

ከግማሽ ክፍለ ዘመን የከፋ የመከራ ዘመናት በኋላ እንኳ አማራ በዘሩ ምክንያት የግፍ ሰለባ መሆኑን  ተቀብሎ ታሪክ የሚጠይቀውን ኃላፊነት ተወጥቶ እንዳያልፍ ሰበብ የሚደርድር  የደነዘዘ ሆዳም አማራ ዛሬም ሞልቷል፡፡ ለምሳሌ ጭራቆች የሚሰሩትን ታሪክ የማይረሳው ወንጀል ለመሸፋፈን አንዳንድ ተአማራው አይደለንም የሚሉ “ግፍ የተሰራባቸው” ሰዎች በሕዝብ መገናኛ ብቅ ብቅ እያደረጉ ሲያስቀባጥሩ ሆዳሙ አማራ “የተፈናቀለው፣ ቤቱ ወይም መቃብሩ የፈረሰው እኮ የአማራው ብቻ አይደለም” የሚል ጅል ሰበብ ይደረድራል፡፡

ጅልና ሆዳም አማራ ለግማሽ ክፍለ-ዘመን በአማራ ዘንድ የተሰራውን ግፍ አሰላስሎ፣ አሁንም የሚሰራውን ግፍ በጥሞና አጢኖ ወደ ፊት የታቀደውንም ቁማር ለመተንበይ የሰፋው ከርሱ ይጋርደዋል፡፡ እንደ ፕሮፌሰር አስራት ያለ ልባም አማራ ግን እንኳን በፊት የተሰራውን ግፍ መርሳት ወደ ፊት የሚፈጠመውን ተንኮልም ጭራቆች ተማቀዳቸው በፊት አስቀድሞ ያውቃል፡፡

፩. የዘር ማጥፋት ወንጀል፡- ከወልቃይትና ራያ የጀመረው የአማራ ዘር ማጥፋት ዛሬ በመላው አገሪቱ በከፋ ሁኔታ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ የዘር ማጥፋት ዘመቻው በባሩድ ብቻ ሳይሆን ወላዶችን በማምከን፣ በጅምላ እያፈሱ በእስር በማንገላታት፣ በማሰደድ፣ ለበሽታ በማጋለጥና ለድህነት በመዳረግ ተካሂዷል፤ በመፈጠም ላይም ይገኛል፡፡

፪. ታሪክን የማጥፋት ዘመቻ፡- የአማራን ታሪክ የማጥፋት ዘመቻው ፊደሉና ቋንቋው ተአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል መጠቀሚያ እንዳይሆን ተመከልከል ጀምሮ ዛሬ ቅድመ አያቶቹ በቆረቆሯቸው ከተሞች ያሉ ቅርሶች በተለያዩ ስበቦች እየተፋቁ እንዲጠፉ እየተደረገ ነው፡፡ ቤተክርስትያኖቹና ሌሎችም ታሪካዊ ቅርሶቹ በቦንብና በመድፍ እየጋዩ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ሲፈጠም ሞኝ ሰው የሚታየው የቤት መፍረስና መፈናቀል ብቻ ነው፡፡ እየተሰራ ያለው ግን የአማራን ታሪክ ማጥፋት ነው፡፡ ታሪክ የሌለው ወይም ታሪኩ የጠፋ ሕዝብ ደሞ ስሩ የተቦደሰ ዛፍ ማለት ነው፡፡

፫. መቀበርያ ማሳጣትና የተቀበረውንም በግንዲደር እየዛቁ የመወርወር አረመኔአዊ ድርጊት፡- በልጅነታችን “የሞተን ሰው የሚያከብሩና የማይነኩ የዱር አውሬዎች አሉ” ሲባል እንሰማ ነበር፡፡ ዛሬ የሞተን ሰው መቀበርያ የሚከለክሉና ሲሻቸውም ስልጣናቸውን ተጠቅመው የራሳቸውን ሰዎች በሚፈልጉት ቦታ በሰፋፊ መቃብሮች ውስጥ እየቀበሩ ሌላውን በተለይም በመሰረታት አገሩ መጤ የሚባለውን አማራ ለመቀበርያ ከአስር እስከ አስራ እምስት ሚሊዮን ብር እሚጠይቁ፤ የተቀበረውንም በልማት ስም በግኒደር እየዛቁ የሚወረውሩ ከዱር አውሬም ያነሱ ፍጡሮች እያየን ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙ ሰው ዘመዱ ሲሞት ከአገሩ ይልቅ ዉጭ አገር መቅበርን እየመረጠ ነው፡፡

አማራ የዘር ማጥፋት ወንጀልን፣ ታሪክን የማጥፋት ዘመቻን፣ መቀበርያ የማጣትንና እሬሳውን በግኒደር የመዛቅ ግፍ መታገል ያለበት በነቂስ ተደራጅቶና አንድ ሆኖ ነው፡፡ በእነዚህ ግፎች ዙርያ አንድ የማይሆን አማራ ከሰውነት የወጣ ከአውሬም ያነሰ ከንቱ ፍጡር ነው፡፡ አውሬ እንኳ ዘሩን የሚያጠፋ ኃይል ሲመጣ ሰበቡን እየደረደረ ሆዱን ሞልቶ ይተኛል ወይም እርስ በእርሱ ይናከሳል ማለት ዘበት ነው፡፡ አይኑ እያዬ ዘሩን አስጠፍቶ፣ ታሪኩን አስፍቆ፣ የመቃብር ቦታ የሚነፈገውና ሬሳው ተፈንቅሎ የሚወረወር አማራ ከእንሰሳም በታች መቆጠሩን ልብ ይበለው፡፡  አማራ በነቂስ ወጥቶ አንድ ሆኖ መታገል ያለበት ለመኖር ብቻ ሳይሆን ታሪኩ እየተገሸለጠ እንዳይጣል፣ መቀበሪያ እንዳያጣና የተቀበረውም በግኒደር እየታፈሰ መወርወሩ እንዲቆም ነው! አመሰግናለሁ፡፡

 

ነሐሴ ሁለት ሺ አስራ ስድስት ዓ.ም.

 

12 Comments

  1. ልክ ነው ጌታዬ ትግሬን ከላይ አገኘሁ ተሻገር፣ገዱ አንዳርጋቸው፣ ዮሀንስ ቧያለው፣ንጉሱ ጥላሁን፣ይልቃል ከበደ፣ደመቀ መኮንን አረጋ ከበደን የመሳሰሉ አተላዎች ጥሎበት ምን ያድርግ? አብይና መለስ ፊት ይሽኮረመሙና በካልቾ ሲሏቸው ይቅለሰለሳሉ ገና ብዙ የአማራ ባንዳ አለ ሰልፍ የየያዘ የአብይን ሹሙት የሚጠብቅ

  2. አዘጋጅ፦

    እኔ በዚህ አምድ ላይ እንዳነበብሁት፣ ፋኖ (አማራ) በዚህ ድርሰት ወስጥ ለተጠቀሱት ዓላማዎችም መታገል ከጀመረ ዓመት አለፈ። ደራሲው ገና መስማታቸው ነው ?

    • አቶ አንድነት አልሰመረ

      ጠብ ያለሸ በዳቦ አረከው እንጅ እንደገባኝ ጠሀፊው የሚያሳሰቡት ዝም ብሎ ሆዱን ሞልቶ አዳሪው የአንተና የኔ ቢጤ እንደ ፋኖ እንዲሆን ነው።
      ከተረብ በፊት ፍርጥ አርገህ ለማንበ ብ ልመድ።

  3. ጎበዝ አደብ ግዙ በአንድ በኩል ትግሬ ዘበርጋንም፤ጫላንም፤መርዳሳንም…..ሁሉንም ሁኖ ያምሰናል በሌላ በኩል እኛም ትእግስት እያጣን በሚመስለን እየተረጎምን እንፈነካከታለን ፡፡እባብነቱን በመጠኑም ቢሆን ከትግሬ ተማሩ እንጅ፡፡ አሁን ትግሬ መለስ ዘራዊን ወዶት ነው? ከነሱ በላይ ኤርትራን እንደሚወድ ያውቁታል ነገር ግ ን እኛ እንዳንሰማው ጠላ ሲጠጡ የውጭ ሰው አለመኖሩን ካረጋገጡ በኋላ ነው አበበ ገላውን ዘር ይውጣልህ ብለው የሚመርቁት፡፡ ጎበዝ ነቃ በሉ እንጅ ሁሉን እግር ጠልፈን አይሆንም፡፡

  4. አቶ ግርማ፦

    ምናልባት የማታውቀው፣ ሆድ አዳሪም አይደለሁ፤ የአንተ ቢጤም አይደለሁ። ጠብ ፈላጊም አይደለሁ። ተረብም አላውቅም። አንተ ያብራራህ የመሰለህ ጉዳይ የዛሬ ዓመት ግድም የሰማነው ነው። የማታውቀውን ሰው ከራስህ ጋር አታነጣጥር ! በግንባር ባገኝህ፣ ያልኸውን ሁሉ አለመሆኔን በደቂቃ አስረዳህ ነበር። ስሜም “አንድነት ሰመረ” ነው። ስሜ የሆድ አደር ይመስላል ወይስ ሌላ መልዕክት አይታይህም ?

    • አንተም እኔም እንደ ፋኖ እየተፋለምን አይደለም። በጣልያን ወረራ ዘመንና በአሁኑ ዘመን ተጋድሎ ያልተሳተፈ ሁሉ አንድም ባንዳ ሁለትም ሆዱን ሞልቶ አዳሪ ሆድ አደር ነዉ። በተረፈ ተረብህን እየተረተርከ ተራቢ አደለሁም ማለት ከሥራዬ ምላሴን እመኑት ማለት ነው።

  5. ወንድም ግርማ፦
    ሳላውቅህ “አቶ” በማለቴ ያንተን ያህል ባይሆንም ተሳስቻለሁ። በጦር ሜዳ ያልተሳተፈ ሁሉ “…አንድም ባንዳ ሁለትም ሆዱን ሞልቶ አዳሪ ሆድ አደር ነዉ።” ስትል አልተሳሳትህም ? ዛሬ በአማራ ክልል ያለ ሁሉ ፋኖ ቢሆን፣ ሌላው ቀርቶ፣ ፋኖን ማን ያብላው ? ከክልሉ ሕዝብ ውስጥ 85% አርሶ አደር ሲሆን፣ ያም ወደ 35 ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ ይሆናል። ከ18 ዓመት ዕድሜ በታች ያለ ጉብል፣ ከ70 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆኑ አዛውንት፣ በሽተኞች፣ እመጫቶች፣ ሐኪሞችና ነርሶች፣ አስተማሪዎችና ከፍተኛ ምሁራን፣ ክልሉን የሚመግቡ አርሶ አደሮችና ሌሎችም በጦር ሜዳ ላይ የሌሉ “ባንዳ” ወይም “ሆድ አደር” ናቸው ስትል በጤናህ ነው ?

    መለስ ዜናዊ በ 1985 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ዩኒቬርሲቲ 41 ምሁራንን ሲያባርርና ዩኒቬርሲቲውን ሲያደቅቅ፣ ኤርትራን ሲያስገንጥልና ሉዓላዊነታችንን አስደፍሮ ወደብ አልባ አድርጎን ትግራይን ጭምር የባሕር በር ሲያሳጣ፣ ወያኔ እንደገባ እንደ 1982 ዓ.ም. ከእሥር የተፈታው ጀግናው ኔልሰን ማንዴላ ዲሞክራሲያዊና ፌደራላዊ መንግሥት በመመሥረት ፋንታ፣ 9 ምርጥ ጎሣዎች ለቀሩት 74 ጎሣዎቻችን ፈላጭ ቆራጭ ገዢ ሲያደርግና ለዛሬዋ የትግራይ ወገኖቻችን ጭምር የከፋ ሞት፣ ስደት፣ መፈናቀል፣ ርሀብ፣ ውርደትና ሰላም ዕጦት ያበቃ ሕገ መንግሥት ሲያውጅ፣ በ1997 ዓ.ም. የቅንጅትን የምርጫ ድምጽ ዘርፎና አፍኖ፣ አያሌ ድምፅ ዝርፊያውን የተቃሙ ወጣቶች በታንክ ሲደፈጥጥና እያሳደደ ሲገድል፣ የቅንጅት መሪዎችንም ወደ እሥር ቤት ሲወረውር፣ በእርሱ እይታ አልተሳሳተም።

    እንዲያውም ትንሽ ዘገየ እንጂ፣ የዩኒቬርሲቲ ምሁራንን ማባረሩ ስሕተት እንደንበረ ተናዟል። አንተም ያው እንደ መለስ ዜናዊ ሥልጣን አይነካም ክርክር አንተም “ባንዳ” ወይም “ሆድ አደር” ብለህ በሕዝባችን ስትፈርድ ከእውነት እየሸሽህ ቢሆንም፣ ለመለስ ዜናዊም ሆነ ላንተ እውነትን መደፍጠጥ አይቻልም። ሥልጣን ለማስጠበቅ ወይም ለመድረክ ክርክር ብቻ ሲባል ያልሆነ አቋም መያዝ አንዱ የአገራችን አስከፊ ችግር ነው። ጓደኞችህም ሳይቀር ይፈርዱብሀል። እግዚአብሔር ይማርህ !

    • ተራቢና ጠብ ያለሸ በዳቦ ብቻ ሳይሆን ያልተፃፈ እያነብክ ለማሰጠላት የምታሴር አሳባቂ ነሀ! የትኛዉ አሰተያየቴ ላይ ነዉ ‘በጦርነት ያልተሳተፈ ሁሉ.,. ‘ ብየ የጣፍኩ?

      በራሱ መቆም የማይችል ወላሻ ድጋፍ ፍለጋ መንገዳገዱ የተለመደ ነው። በተለያየ መንገድ ተጋድሎ በማድረግ ላይ ያለዉን ከቡሩን የአማራ ሕዝብ በማሳበቅ ድጋፍ ለማግነኘት መወጣጠሩን ተዉና ዝም ብለሀ ሆድህን ሞልተሀ እደር።

    • ይመቻችሁ። ገጣባ ሃሳብ ስታንከባልል እድሜ ልክህን ኑር። እኔ የጻፍኩት ሲፈለግ የሚገኝ ጉዳይ ነው። ዘ ሃበሻ ሃሳቤ አይመጥንም ብሎ ማንሳቱ የኤዲቶሪያል ክፍሉን እንበለ ፍርድነትና ከመንጋ ጋር ነጓጅነትን ያሳያል። ግራም ነፈሰ ቀኝ እኔ ከጊዜ አሸን ጋር አብሮ መብረር አይመቸኝም። ፋኖ የአማራ ህዝብ ጠላት እንጂ ወዳጅ አይደለም። ሂዱና በየስፍራው የሚሰሩትን እዪ፤ ህዝቡን ስሙ። በስማ በለው ወሬ ሰክራችሁ ሰው አታስክሩ። እውነቱና ጉራው ለየቅል ነውና! የአቶ ስመረ በእኔ ሃሳብ መነሳት ደስታውን መግለጡ የሚጠበቅ ነው። ጡሩንባ ነፊው ሁሉ ጋዜጠኛ በሆነበት በአሁኑ ዓለም ላይ የሚቸግረው እውነትን ማሳየት እንጂ ግርግር መፍጠር አይደለም። ራሱ ተደናብሶ ሌላውን ሲያደናብስ ከኖረ ሰው ምን ይጠበቃልና!

  6. ተስፋ፦
    ፋኖን አጥላልተሀል። ፍረጃ ብቻ እንጂ መረጃ አልሰጠኸንም ።

    እኔ ፋኖም አይደለሁም፣ ፋኖም አላውቅም፣ አንድ ሣንቲም ለፋኖም ሰጥቼ አላውቅም። ግን ከመንግሥትና ከግልም መገናኛ ብዙሀን እንደማየውና እንደምሰማው፣ አንተ የምትለው እውነት አይመስልም። እውነት ቢሆን ኖሮማ፣ ፋኖ ዛሬ ያለው ደረጃ አይደርስም። ሌላው ቀርቶ፣ የመከላከያ መኮንኖችና ወታደሮችም አይቀላቀሉትም ነበር። ባላገሩም ብዙዎች እንደሚያምኑት፣ ሞኝ አይደለም፣ እንደ እኛ ነው። ጥቅምና ጉዳቱን ያውቃል። ባያምንበት፣ እንደዚሁ ተጎትቶ ጫካ ውስጥ ከፋኖ ጋር መኖር አይመርጥም። መደቡ ላይ ተቀምጦ፣ ጠላውን በዋንጫው/ጥዋው እየጠጣ፣ ሰነፍ ቆሎውን እየቆረጠመ፣ ከዘመድ አዝማድ ጋር በሞቀ የድሀ ጎጆው መኖሩን ትቶ ለምን ዱሩን መረጠ ብለህ መጠየቅ ይገባል። “ጥራኝ ዱሩ፣ እረ ጥራኝ ዱሩ፣ ላንተም ይሻልሀል ብቻ ከማደሩ።” ሲባል እኮ አመጣጡ ከመከፋት፣ ከመገፋት፣ ከሕልውና አደጋ ጋር የተገናኘ ነው። ዛሬ በአሜሪካ ታላላቅ ተቋማት ውስጥ ያሉ ድንቅ ባለሙያዎች እኮ ባመዛኙ የባላገሩ ልጆች ናቸው። ዕድሉ ጠፍቶ ነው እንጂ፣ መሰሎቻቸው በባለጉሩም ውስጥ አሉ !!!!

    ባላገሩ የኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ምሰሶ ነው፣ ጠላት ቢመጣ የሚዘምት እሱ ወይም ልጁ ነው። ይህን የሚያውቁለት እንደ አባ ዳኘው ያሉ መሪዎች ነበሩ። ግን የእኔ ቢጤዎች ከተማ ሲገቡ ያን የኢትዮጵያ ምሰሶ ይረሱትና በእሱ ትከሻ መንደላቀቅ ይመርጣሉ። ባላገሩ፣ የዛሬ 3000 ዓመት በመጣ ሞፈር-ቀንበር፣ በአንድ በኩል በሬውን ማረሻ ከማስጎተቱ ሌላ ሞፈር ቀንበር አሸክሞ ሲያደክም፣ በሌላ በኩል አራሹ በየደቂቃው ጭቃ በማራገፍ ዞሮ በመጣ ቁጥር ሲደክም፣ በሬና አራሽ ማረሱ ላይ ጉልበታቸውን በሙሉ በማይጠቀሙበት ኋላ ቀር መሣሪያ ለሺ ዘመናት ሲኖር አንድም በV8 መኪና የሚምነሸነሽ የአስተዳደር ሹም መሣሪያውን ሊያሻሽለው ሞክሮ አያውቅም። በዚያ ላይ ኋላ ቀር ማረሻችን አፈር ስለማይገለብጥ አረም እንደገና ብቅ ይልና ለመንቀል ብዙ ያደክማል፣ ማረሻውም ወደ ውስጥ ብዙ ስለማይገባ ምርቱ ይቀንሳል። ታዲያ ዛሬ ከምንሰማው፣ ያ የተረሳው ባላገር ነው የፋኖ ዋና ደጀን።

    የዚያ የተረሳው ባላገር ችግር ይኸ ብቻ አይደለም፣ መሬት እንደ ዛሬ 50 ዓመቱ ሰፊ ሳይሆን፣ የበሬ ግንባር የምታህል ነች ። መሬቱም ተበልቶ፣ ምርታማነትም ብዙ አላደገም፣ ማዳበሪያም ውድ ሆነ። ስለሆነም ምርቱ መሬት በምትጭር ማረሻ በጣም ቀነሶና አራሹ እንኳን ለገበያ የሚሽጥ ትርፍ ምርት ሊኖረው፣ ለራሱም ቤተሰብ የሚበቃ አልሆነም። ገዢዎቹ ግን የሥራ ድርሻቸውን ረስተው ከአራሹ በተሰበሰበ የድሀ ገንዘብ በከተማ ሲምነሸነሹ ችግሩን አልተገነዘቡለትም። ዛሬ ዛሬ ደግሞ ትምሕርት ቤት ከፈትንልህ እያሉ የባላገር ልጅ 12ኛ ክፍል ደርሶ ከተፈተነ በኋላ 5 በመቶ ብቻ አለፈ ተብሎ፣ በያመቱ ወደ 600000 የወደቀ የድሀ ባላገር ልጅ የሚበላውም ያጣል። ለዚህም ተጠያቂው፣ ስንት አገር ገንቢ አማራጭ በግብርናውም ሆነ በትምሕርቱ ዘርፍ እያለ፣ አገር ያራቆተውና ትውልድ ያኮላሸው አስተዳደሩ በመሆኑ፣ ባላገር አስተዳደሩን ጠልቶ ፋኖን ቢደግፍ ይደንቃል?

    ተስፋ፣
    በዘመናችን ደግሞ ግልብ ልሂቃን ያመጧቸው ሌሎች ችግሮችም አሉ፦ ለ83 ጎሣዎች ቢበዛ 9 ጎሣ ብቻ የሚገዛባቸው 9 ክልሎች ብቻ ፈጥሮ፣ የቀሩትን 74 (83 -9 = 74)ጎሣዎቻችንን ክልል-የለሽ አድርጎና ለዘጠኙ ባለክልል ጎሣዎች ተገዥ አድርጎ፣ የመንግሥት ሥልጣን በሙሉ በማዕከል በአንድ ቁጥጥር በማይደረግበት ቡድን እጅ ገብቶ፣ የሕዝብ አቤቱታ የማይሰማበት ጨቋኝ ፌደራልም ሆነ ዲሞክራሲያዊ ያልሆነ ሕገ መንግሥት አለን። ሰው እንደ ከብት በክልል የተገደበበት ሥርዓት አለን። ሰው በዘርና በሃይማኖት እየተመነዘረ የሚጠቃበት ሥርዓት አለን። በዘር እየተለየ ከቤት ንብረት የሚፈናቀልበት ሥርዓት፣ አጽመ ዕርስት ተቀምቶ ባለእርስቶች ተፈናቅለው ወይም ተገድለው ለባለጠመንጃ የሚሰጥ ሥርዓት አለን። ዋለልኝ የሚባል ግልብ የአማራ ወጣት ባመጣው ፈሊጥ ጩልሌዎች እየነገዱ ከበርቴ የሚሆኑበት ሥርዓት አለን። ብሔር ብሔረሰቦች የሉዓላዊ ሥልጣን ባለቤት ናቸው ተብሎ ቢደነገግም፣ ለጩልሌዎች የዝርፊያና የመንደላቀቂያ አገር ከማመቻቸት ሌላ፣ ለአንዳቸውም ሉዓላዊ ሥልጣን ያላጎናጸፈ ሥርዓትም አለን። ታዲያ የአገሪቷ አብዛኛው ወገን የሆነው ባላገር የዚህ ሁሉ ግሳንግስ ተሸካሚነቱ በቃኝ ብሎ ፋኖን ቢደግፍ ይገርማል ? በእርግጥ፣ በፋኖ ስም የመንደር አውደልዳይ ሌባ እንዳለ ፋኖዎችም ተናግረዋል። ፋኖም መላዕክ አይደለም !

    ተስፋ፣
    አንዱ ዋናው ችግር፣ የሹም ቁጥጥር የሌለበት የአገዛዝ ሕገ መንግሥት እንዳለን አለማወቅ ነው። የደርግ ቀበሌ ሕገ መግሥቱ የቀበሌ ሹም ጠመንጃ ነበር፤ ባለጠመንጃው ሲፈልግ ይገፈትራል፣ አለዚያም እንደ ጥጃ ጎትቶ ያሥራል፤ ከመሰለውም ይገድላል። ሕገ መንግሥታችንም ለዚያ ዓይነት ተግባር አመቺ ነው። ማንም ሹም ምንም ወጀል ቢሠራ አስተማማኝና ፈጣን መቅጫ የለም። ስለዚህ የእኛ ሹማምንት ያለምንም ስጋት ሕግ ይጥሳሉ፣ ሕዝብ ያጎሳቁላሉ፣ ድሀ ይበድላሉ። በደል ሲበዛ ደግም በደል አንገፈገፈኝ የሚለውን ፋኖ ይፈጥራል። ዋናው ተበዳይ ደግሞ ከሕዝባችን 85 በመቶ የሆነው ባላገር ነው። ሕገ መንግሥት ዲሞክራሲያዊ ሲሆንማ፣ የቅርቡ የታላቋ ብሪታኒያ ሊዝ ትራስና ቦሪስ ጆንሰን ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ተባርረው የለም ?

    የታላቋ ብሪታንያ ዓይነት ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ቢኖረን ኖሮ ፋኖም አይኖርም። ዋናው የሚጎድለን እርስ በእርስ የማያጋድለንና የማይከፋፍለን፣ ሹሞችን ባግባቡ መቆጣጠር የሚያስችለን፣ ኔልሰን ማንዴላ ከ27 ዓመት እሥር ወጥቶ በ 1981 ዓ.ም. እንዳደረገው፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በእኩልነት የሚስማማበት ዲሞክራሲያዊ ሕገ መንግሥት ማዘጋጀት ነው። ፋኖም ይህን እንደሚረዳ ተስፋ አለኝ።

  7. መረጃ አንድ – ታጣቂዎች (ፋኖዎች) አንድ አውቶቡስ ያስቆሙና ሁላችሁም ግራ እጃችሁን ከፍ አርጉ በማለት ተሳፋሪውን ይጠይቃሉ። ተሳፋሪም ሊያፋክሩን ነው ብሎ እጅን ያነሳል። የሆነው ግን ሌላ ነው። አንደኛው ታጣቂ እየዞረ ቀለበት በእጃቸው ላይ ያለውን ሁሉ አስቀልቆ ወሰደ። ፋኖ የሌቦች ጥርቅም ነው። ከተማ ያዝን ያን ሸኘን የሚባለው ሁሉ የተጋነነና ህዝብን ለማሸበር የሚደረግ የድርቡሾች ሽኩቻ ነው። አንድም የአማራ ተማሪ አይማርም። የሚያስተምሩትንም እንገላለን የሚል የክፉዎች ስብስብ ፋኖ ነው። አውቃለሁ ደጋፊዎቻቸው እንደሚንጫጩ። ጥሩ ነው ተንጫጩ። ባንክ ዘራፊና ሰው አፋኙን ፋኖ እኔ ፋኖ ነው አልልም። የአማራን ህዝብ ነጻ አውጣለሁ የሚል ድርጅት የአማራን ህዝብ ለስቃይና ለመከራ አይዳርግም። ፋኖ ዓላማ ቢስ፤ በተናጠል የሚሻኮት፤ ህብረት የሌለው በዚህም በዚያም ብቅ እያለና መንገድ እየዘጋ ህዝባችን የሚያሸብር ከቀደሙት የፓለቲካ ሙታኖች ክፋት የዘገነ፤ ከውድቀታቸው ያልተማረ ስብስብ ነው።
    የሚያሳዝነው የዘሃበሻም ነገር እኔን አልጣመኝምና ሃሳቡ መለጠፍ የለበትም በማለት ማንሳቱ ነው። ዘሃበሻ ሊረዳ የሚገባው በቪዲዪም ሆነ በጽሁፍ በድህረ ገጽ ላይ የሚለጥፋቸው ነጻ አስተያየቶችም ሆኑ ሌሎች ጉድለት እንዳለባቸው ነው። እኔ ፍቱን መድሃኒት ነኝ ማለቱ ተንጋሎ መትፋት ይሆናል። ስንት በግልጽ ህብረተሰብን የሚሳደቡና የተወላገደ ሃሳብ የሚያጋሩ ድውያን አስተያየትን ሲያካፍለን የኖረው ዘሃበሻ ዛሬ ምን ታይቶት የእኔን ሃሳብ እንዳሽቀነጠረው አልገባኝም። ግራም ነፈሰ ቀኝ ውስልትና ያልነካው ስፍራ ያልገባበት ቤት የለምና ጉዳዪ አንባቢ አይቶ ቢፈርድበት መልካም በሆነ ነበር። ያ ግን አልሆነም። መሸራገድና በብሄር ፓለቲካ መሰለፍ የጊዜው የመለያ ማሊያ ሆኗልና!
    ባጭሩ እኔ የፋኖን ትግል እንደ ትግል አላየውም። እንደ መኖሪያ ብልሃት ፍለጋ እንጂ። እርግጥ ነው ጥቂቶች ግፍ አንገሽግሿቸው በረሃ የወጡ አሉ። የእነርሱ ድምጽ ግን አይሰማም። ከሰልፉ ወደኋላ ተደርገዋል። በምን ሂሳብ ነው ፋኖ ከወያኔና ከሻቢያ ጋር አብሮ የሚሰራው? ምን ሊያተርፍ? ለሃገሪቱ ውድቀት ሻቢያና ወያኔ ቀዳሚ ምክንያቶች አይደሉም? አሁንስ ምድሪቱን ለመፈረካከስ ከውስጥና ከውጭ ሃይሎች ጋር እየዶለቱ አይደለም? ታዲያ ልቡ እስኪወልቅ ኢትዮጵያ|2| የሚለው ፋኖ ካፈረሷትና ካፍረከረኳት ጋር ጥምረቱ እንዴት ይዋጠዋል? ቅርሻታም ፓለቲካ!
    የጊዜው አለቆቻችን ኦሮሞዎቹ በሰው ላይ የሚፈጽሙት ግፍ ሰማይ ጠቀስ እንደሆነ በምድሪቱ በየቀኑ በእነዚህ የብሄር ልክፍቶች የሚፈጸመውን ግፍ ማየትና መስማት ብቻ በቂ ይሆናል። አዎን በጭፍን ጠ/ሚሩን መልአክ በማድረግ ገትረው የሚከራከሩ አሉ። ይህ ግን ወልጋዳ እይታ ነው። በወያኔም ጊዜ የግፉ አበጋዝ ነበር፤ አሁንም አላቅም ይበል እንጂ ሰው ከሞተ ሬሳ ጋር አብሮ እንዲታሰር የሚያደርግ እርሱ የሚመራው ብልጽግና ነው። ግፈኞች ዛሬን እንጂ ነገን አያዪም። ለኦሮሞ ነጻነት በማለት በኦነግ – ሸኔ ስም የሚዘርፈውና የሚገድለው ድርጅት ለኦሮሞ ህዝብ ሳይሆን ለራሱ የሚኖር የሽፍታዎች ስብስብ ነው። የኦሮም ህዝብም ሆነ ሌላው የሃገራችን ህዝብ በታጣቂዎች ጉልበት ነጻነቱን ማግኘት አይችልም። በመግባባትና በሰላም በመነጋገር እንጂ! ያ ቢሆን ኑሮ ዛሬ ትግራይና ኤርትራ የምድር ገነት በሆኑ ነበር። ግን ሰው ከአውሬ እንደሚሸሽ ከፊትና ከህዋላ እየተተኮሰበት የሚሮጥባት ሃገር ሃገረ ኤርትራና ኢትዮጵያ ናቸው። ትርፍ የለሽ የብሄር ፓለቲካ! ራሱ ተናክሶ ሌላውን የሚያባላ ፓለቲካ – አይጣል ነው። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

193589
Previous Story

ብጹዕ አቡነ አብረሃም በቤተ ክርስትያን ውስጥ ላሉ የእናት ጡት ነካሾች ሌባዎች ጉቦ ተቀባዎች አንድ ሊባሉ እንደሚገቡ ፓትርያርኩ ባሉበት አሳሰቡ!

193616
Next Story

“ምርኮኞችን ተረከቡን” ፋኖ

Latest from Blog

blank

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ
blank

ፖለቲከኛው አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት ፖለቲከኛው አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል
blank

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ
blank

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop