ቅዳሜ ነሐሴ 11 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ውጥረትና መካረር የበዛበት የህወሃት ፖለቲካዊ ተቃርኖ ልዩነቶች አሁንም ጎልተው መታየታቸውን ቀጥለዋል፡፡
ይህን ተከትሎም የህወሃትን 14ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በውዝግብ ውስጥ ሆኖ እያከናወነ ያለው የነ ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል ቡድን አዲስ ውሳኔ ማስተላለፉ ተሰምቷል፡፡
የህወሃት ሊቀመንበር ቡድን ዛሬ ባወጣው መግለጫም በ14ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ያልተሳተፉ የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ከዛሬ ነሃሴ 11 2016 ዓ.ም ጀምሮ በየትኛውም መድረክ በህወሓት ስም እንዳይቀሳቀሱ ማገዱን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ይህም የታገደው ቡድን ማለት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራና 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትን የያዘ ሲሆን በህወሃት ስም የሚደረግ የዚህ ቡድን እንቅስቃሴ እንደማይታወቅ በሊቀመንበሩ ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል በኩል የወጣው መግለጫ ያመላክታል፡፡
ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰአት ድረስም በአቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን በኩል ምላሽ አልተሰጠም፡፡
አዲስ ማለዳ
ጌቾ ሸቤ መግባቷ ቁርጥ ሁኗል የሚያድናት የለም አሁን ከትግሬነቷ በላይ ራያነቷ ይመዘዛል። እዩኝ እዬኝ ያለ ደብቁኝ ደብቁኝ ይላል እሉ ዶር አሸብር አሁን ማን ሊያድነው ይችላል? ያ ፉከራ ያ ስድብ ጌች ስራህ ያውጣህ የኢትዮጵያ አምላክ ስራው ብዙ ነው ነብስ ገዳይና ተንኮለኛ ትግሬ የእጁን ማግኛቱ ቁርጥ ነው።
አይ ወያኔ ብሎ ብሎ ከራሱ ጋር በግልጽ መባላት ጀመረ? ለእልፍ ጉባኤ ወያኔ ቢጠራቀም በሽታው ራሱ ስለሆነ መዳን አይችልም። ወያኔ ከአሁን በህዋላ እንኳን በጉባኤ በሱባኤም መዳን አይችልም። ለስልጣን ያላቸው ፍቅር 50 ዓመት ሙሉ ይዞ እያንገላታቸው ይኸው ዛሬ ላይ ደርሰዋል፡ ሲጀመር ብሄርተኞች የጭንቅላት በሽታ አለባቸው። ከራሳቸው ወገን አልፎ ከዚያም ባሻገር ከራሳቸው አውራጃና መንደር ውጭ ሌላው ሁሉ ሰው መስሎ አይታያቸውም። ይህ የጠባብ ብሄርተኞች በሽታ ከሃገር አልፎ በውጭም እርስ በእርስ ሲያጋድላቸውና ሲያቧቅሳቸው እያየን ነው። በዚህ ሁሉ ግን ዛሬም የሚነግድበት የትግራይ ህዝብ ነው የሚያሳዝነኝ። አሁን ለሁለት መስመር የተሰነጠቀው ጨካኙ ወያኔ በሌብነት የተካነ፤ በደም የተነከረ፤ ለትግራይ ህዝብ ደንታ የማይሰጠው የራሱን ጥላ የሚጠራጠር ስብስብ ነው። ዶ/ር ደብረጽዪን በጽህፈት ቤቱ ምድር ለምድር የሚሄድ የማምለጫ ዋሻ የሰራው ራሱን ባያምን ነው። ወያኔ ከሃገር ተባሮ በትግራይ ውስጥ ከተወሸቀ ወዲህ የገባበት ሃበሳ እግዚኦ የሚያሰኝ ነበር። ግን የአልባኒያ ጠማማ ፓለቲካ የተቃመሱት እነዚህ ሽንኮች ጉባኤውን ትተው ሱባኤ የሚገቡበት ጊዜ ነበር። ያ ግን አይሆንም። በቁስ አካል እምነት የተበከለ ሰው ዓለምን የሚያይበት አይኑ ሸውራራ ነው።
አሁን የጌታቸው ቡድንና የደብረጽዪን ቢባል የልጆች ጫወታ ቆይቶ የሚፈርስ እንጂ የግራውም የቀኙም ለትግራይ ህዝብ የሚያደርገው አንድም ነገር አይኖርም። ለዚህ ነው የሃበሻ ፓለቲካ የውታፍ ፓለቲካ ነው የምንለው። አንድ ጋ ሲጠገን ሌላ ጋ ያፈሳል። ህብረት አንድነት መስማማት መቻቻል የሚባል ነገር የለውም። እኔን ብቻ ስሙ! አራጊ ፈጣሪው እኔ ነኝ የሚሉ ቶስቷሳ ጠበንጃ አንጋቾች የስንቱን ቤት እንዳጨለሙት ታሪክ መዝግቦ ይዞታል። የወያኔ ስብስብ ስለ ትግራይ ህዝብ ደህንነት ይገደዋል? በጭራሽ! እነ መምህርት ብርክቲ ተስፋማሪያም ሲገደሉ፤ ብዙዎች ሲዘረፉ፤ ሴቶች ሲደፈሩ የወያኔ ህግና ደንብ የት ገባ? ያለፈ ታሪካቸውን ትላንት እንደሆነ በማድረግ አኝከው እየዋጡ በመሸ ጊዜአቸው ላይም ከተንኮል የማይርቁት እነዚህ ተኩላዎች አፈር ሲመለስባቸው ብቻ ነው ግፋቸው የሚመክነው። እስከዚያው ትግራይንም ሃገርንም እያተራመሱ ይቆያሉ። የአቶ ጌታቸው መታገድም ሆነ የደ/ጽዪን ድንፋታ አይተነዋል ቀን ሲመሽ ዋሻ ለዋሻ እንዳንከራተታቸው። እኔ ግን ለ 50 ዓመት ልጆቹንና ኑሮውን ለወያኔ ሲገብር የኖረው የትግራይ ህዝብ አንድ ቀን ሆ ብሎ ከተነሳ አንድም የወያኔ ታጣቂ አያስቆመውም። ያ ጊዜ የተቃረበ ይመስለኛል። እስከዚያው በእነዚህ የፓለቲካ ጅላፎዎች እየተገፉና እየተገደሉ መኖር ግድ ሊሆን ነው። አታድርስ ነው።
አንተ የምትለው ችግር ከደረሰበት ትግሬ እራሱ ፈንቅሎ ይነሳል ፈንቅሎ ካልተነሳ ተስማምቶታል ማለት ነው ።ቀደም ሲል ዘርፈው የሰጡት ጥሪት ብዙ ዘመን ያቆየዋል ማለት ነው። የነሱና የኤርትራ ልጆች አያገባችሁም ጥጋብ በጥጋብ ላይ ነን እያሉን ነው አንተን የመሰሉ ደግሞ በሰው ያልደረሰ ደርሶባቸዋል አልቅሱላቸው ትሉናላችሁ እኛ የቱን እንመን?