October 20, 2023
4 mins read

በኢትዮጲያዊያን ላይ ሰቆቃ የሚፈጽመው የአብይ አህመድ ምንደኞች ይጋለጡ

56gggggg 1 1የህዝባችን ሰቆቃ ሳይገዳቸው ለስልጣን ለዝና ለዩ ጥቅም ወይም በዘር ከወያኔ እስከ ኦነግ ብልጽግና የሚያሸረግዱ የሃይማኖት መሪ ሆኑ ምሁር ተብዬ ያለምንም ርህራሄ መጋለጥ ይገባቸዋል::

የምንወደው ዘ-ሐበሻ ይህን ሃገራዊ ተጋዳይነት የሚደነቅ ነው ይበል ያሰኛል  ወንድማችን  አልዩ ተበጀ ቀጥልበት:: በያልንበት ያሉት መምከር ካልተመለሱ ማግለል የምንችልባቸው ብዙ መድረኮች አሉ:: ከእነዚህ ህሊና ቢሶች አንዱ ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም በተደረገው ጥረት ተገቢ ተግሳጽ ቀርቦለት በሚዋደቁት የፋኖ ወጣቶች ላይ ልቅ አፉን ስለቀጠለ በየሆቴሉ በየመናሀሪያው ፊት የሚነሱት የቁርጥ ቀን ልጆች ተነሰተዋል:: ወደፊትም መቃብሩ ላይ የሚቆም ቅን ኢትዮጲያዊ እስከማይጠፋ ድረስ ማጋለጡ ማራቁ ይቀጥላል:: የሃይማኖት መሪዎቹም ባለፈው ጉደኛይቱ አዳነች አበቤን ያሞካሹት ካህን ከእጃቸው ስጋወደኑ ያለመቀበል ድረስ መመናን በመትጋት ላይ ሲሆኑ የጰኔጠቆስጤው ፓስተር ጻድቁ አብዶ የወንጌላዊት ቄስ ደረጀ ቄስ  በያልነበት በተለይ የአሜሪካ ፓስተሮች ለምእመናንም በማሳወቅ ላይ ነን ልክልካቸውን ነግረናል:: የግፈኛው አብይ አፈቀላጤነቱን ካላቆሙ በሚቀጥለው ምርጫ ይነሱ ዘንድ ምእመናኑን በመቀስቀስ ላይ ነን::

የድንቅ ሃገር ወዳድ ሙፍቲህ ኢንድሪስን የተረከቡት ሃጂ ቱፋም በቀጥታ የተነገራቸው ሲሆን ቅን ሙስሊም ኢትዮጲያዊያን የመጅሊስ ጉባኤ ላይ በተለይ ወለዮቹ የሚያቀብሩብት ብዙ ብርቱ ጥያቄዎች መኖራቸውን ያለሁበት ግሩፕ Interfaith Coalition በማህበራዊ ሚዲያ እየተገረው ነው ቅን ሙስሊሞች ትናንት ድምጻችን ይሰማ በጋራ ያሰማን በርቱ:: አሜካኖቹና የአውሮፓ ህብረት የተፈጸመው ዘር ማጥፋት አብይን ከስልጣን የሚያስወግድ በመሆኑ አብይ ከወደቀ ሃገሪቱ ትፈርሳለች በጥገና ለውጥ ይካሄድ ያሉ የሚደራደሩ የሁሉም ፓልቲካና ማህባራት ተወካዮች ምቃውም ይኖርባቸዋል

የሰው መብት አስከባሪዎች ቆይታ ጉብኝት በዚሁ ስጋት የታገደውን ይህን በብርቱ ላቀረቡት የኣውሮፓ ህብረት በዚያ ያላች ሁ በተለይ ብራሰልስ ለሚታረደው ህዝባችን ሞግቱ:: የተገፋው የኢትዮጲያ ህዝብ በተለይ ያቸንፋል ጨቁዋኝ ፈሮንን ባህር ያሰመጠ ት እቢተኛው ናቡከደነጾርን ሳር ያስበላ ጌታ በግፈኞቹ የኦሮሙማ መሪዎች ላይ ይፈርዳል::

ኢትዮጵያ በነጻነትና በአንድነት ለዘለዓለም ትኑር!!

ደጎን ሞረቴው

2 Comments

  1. ፓስተር ዲጎኔ ሞረቴው አቶ ዳንኤል ክብረትን ረስተውት ነው? አረጋዊ በርሄ፤ሌንጮዎችን፤ዲማ ነገዎን፤መራራ ጉዲና፤በየነ ጴጥሮስ የመሳሰሉትን ጨምረው ቢከኩልን፡፡

  2. ሰው አልማርያምን ይቀየማል? ጸጉሩን ሳየው ቀደም ሲል በአሜሪካ ፋኖነትን ለመጀመር ሳያስብ አልቀረም፡፡ እስቲ በዚህ እድሜ እንዲህ ብድግ ብሎ ጸጉርን ማጎፈር መብት ነው? ወይስ የጤንነት ወይስ የኢትዮጵያ አምላክ አቅጣጫውን አስቶት? ጸጉሮቹ ሳይሳሱ ቀደም ብሎ ቢሆን አንድ ነገር ነበር፡፡ እንደው ትምህርት ሲበዛ አናት ላይ ሳይወጣ አይቀርም የሚባለው እውነት ሳይሆን አይቀርም፡፡ አያቴ ይቅርብህ ድቁና ተማር ያለችኝ አሁን ት ዝ አለኝ፡፡ ፕሮፌሰር ማሞ ሙጨም ጸጉራቸው እንደ ጥላ ሁኖ ሰው ባጠገባቸው ለመሄድ አንደ ሜትር ያስፈልገው ነበር፡፡ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ለዚህ አልታደሉም እንጅ ሹሩባ ይሰሩት ነበር፡፡ ለሹሩባው ባይታደሉም ወጣትነትን በቋንቋቸውና በሸሚዛቸው ሊያሳዩ ጥረት ያደርጋሉ፡፡ እነ ሎሬት ጸጋዬ አይነት የሃገር አድባር ወስዶ እነዚህን ይልቀቅብን? ዶር ብርሃኑ ባለፈው አሰብን ለማስመለስ በግልግል እንደቀሩ ሰማሁ እንዲህ አይነቱስ ድፍረት ሊመሰገን ይገባል ናፖሊዎን ነው ሁል ጊዜ አሳማ ሁኖ ከመኖር አንድ ቀን አምበሳ ሁኖ መሞት ይሻላል ያለው? እንደው ፈረንጅ ካልጠቀስን ያወቅን አይመስለንም እንጅ ፊታውራሪ ጎሹ ጥዋት ማታ የሚተርቱት ተረት ነበር ግን ማን ይጥቀስላቸው? አይ የኛ ነገር፡፡

    በር ወደ ኋላ፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

186616
Previous Story

አየር ወለዱ ኮማንዶ የከንቲባዋ ቦዲ ጋርድ የነበረ ፋኖ ! | ”በቅርቡ አዲስ አበባ አራት ኪሎ እንገባለን

186601
Next Story

በኢትዮጵያ ለተከሰተው ረሃብ ግሎባል አሊያንስ የድጋፍ ጥሪ አደረገ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop