ይድረስ ለአክራርያን – ኢትዮጵያዊነት ያሸንፋል –  ከአባዊርቱ

ይድረስ በአገር ውስጥም ሆነ ከውጭው አለም በክፋት ለምትራወጡ ወገኖቼ። መቼስ ወገን ናችሁና እንኳን ለፈረንጆቹ ገና በአል አደረሳችሁ በውጭው ላላችሁት።
እንዲህ ነው ጉዳዩ!
ያለኝ መልእክት በጣም አጭር ነውና በጥሞና አድምጡኝ። እስካሁን ኢትዮጵያዊነትን ሆን ብላችሁ ከውስጥና ከውጭ ገዝግዛችሁ አልተሳካላችሁም። ወደፊትም አይሳካላችሁም። ይህን ቅን መሪ ቆም ብላችሁ መርምሩ። እንደናንተ ሙዋርተኛና ክፉ ሰው አይደለም። የወጣበትን መንደር ለይቶ የሚያውቅ፣ የወደፊቱን አርቆ የሚመትር ጀግና ሰው ነው ያገኘነውና እባካችሁ ቆም በሉና አስተውሉ። ይህ መልእክት በተለየ ለአማራውና ዖሮሞ አክራርያን ነው። ወያኔዎቹን አይመለከትም። እናንተን ፍርዱን የሚሰጣችሁ ፈጣሪ ብቻ ነው። የሰው እርጉሞች። ምቀኞችና ሰብአዊነት የጎደላችሁ ክፉዎች። ከ 28 አመት በሁዋላም ትክክል ነን ባዮች። አገራችንን ምስቅልቅሏን አውጥታችሁ ዛሬም አለኛ በቀር መዳኛ የላትም የምትሉ መካሪ ያጣችሁ ደመነፍሶች። ፈጣሪ ይቅር አይበላችሁ እንኩዋንስ ወገን።
አክራርያን ወገኖች። በጣም ግራ የሚገባኝ ብዙዋቻችሁ የውጭውን አለም አይታችሁዋል። ለምን የሰለጠነ የአክራርያን ፓርቲ በህብረት መስርታችሁ በጋራ አቢይን አትሞግቱም? በሀሳብ ሞግቱኝ እኮ ነው የሚሉት ሰውዬው። በራሳችሁ ቁሙና ሞግቱ። ወያኔ ስር መርመጥመጡ ይቁም ። እራሳችሁን ቻሉ እስቲ። በፌዴራሊስት ስም ከነሱ ጋር ከመርመርመጥ ለምን የራሳችሁን የጋራ ሸንጎ መስርታችሁ አትሞግቱም? ከተጫረሳችሁም እርስበርስ አድርጉት። የደሀውን መስጊድና ቤተክርስትያን አትንኩ ወይም አባሪና ተባባሪ አትሁኑ። የደሀውንም ደም በከንቱ እንዲፈስ  አታድርጉ ወይም በቀጥታም ይሁን ተዘዋዋሪ አትተባበሩ።  ጀግና ከሆናችሁ ማ ምን እንደሆነ ትተዋወቃላችሁና እዚያው ተጨራረሱ። የኢትዮጵያን ህዝብ ለቀቅ አድርጉት። በዚች አመት ተኩል፣ ሰው ተዘቅዝቆ በተሰቀለባት አገር እነሆ ሳተላይት ወደህዋ መጠቀች። የኡትዮጵያ አምላክ አያሸልብም የምንለው የዋዛ አይደለምና። ይህንኑም ደግሞ አቃቂር የምታወጡትን ታዝቤአለሁ። ሳተላይቱ ከሱሉልታም ትሁን ከእንደርታ ለታዳጊዎች ሌላው ቢቀር ፖዘቲቭ ኢነርጂ ነች።  ኢትዮጵያዊነት ከሁሉም በላይ ነው። የሚያምርብንም እንደዛ ስናስብ ነው። ክብሩ ይስፋና አቶ ለማም ይህው ወደ ህሊናው ተመለሰ ማለትን ሰማሁ። እውነት ከሆነ ደስ ይላል ። እንደሚመለስም ተንብዬ ነበር። እናንተ አክራሪ ገልቱዎች አሳስታችሁት እንጂ አጀማመሩ መልካም ነበር።
ውድ አክራርያን!
ሁሉን ሞከራችሁ። ኢትዮጵያ እንዲህ እንዳሰባችሁት የምትከስም የዋዛ አልሆን አለችባችሁ። እንግዲህ ምን ቀራችሁ? እውነት ህዝቡ መተላለቅን ነው ወይስ አብሮ ድህነቱን መጋፈጡ ይቀለዋል? እንደናንተ ፖለቲካውን ጥርሴን ባልነቅልበትም እንደው ከላይ ሳየው የምትከተሉት መንገድ በፈጣሪም ይሁን በሰው ዘንድ አያዋጣም። እስቲ ሰከን በሉ። እስከመቼስ እነዚህ በቁም ያሸለቡ ወያኔዎች ይጯወቱባችሁ? በተለይ የሚያቃጥለው የዖሮሞ ምሁራን ተብዬዎች ዬትኛውን ምሁር አክብረው ያውቃሉና ነው መቀሌ ኮንፈረንስ እየሄዳችሁ ስንት አስርተአመታት በህዝባችን የቀለዱትን ሰዎች በስመ ሳይንሳዊ ኮንፈረንስ ስታሽቃብጡ የሰነበታችሁ? ምን ደህና ነገር ከነዚህ ሰዎች ጠብቃችሁ ነው? የራሳቸውን ሰዎች መተንፈሻ ኦክሲጂን ከልክለው ህዝቡ እንዳይሰበሰብ እያገዱ፣ ጀግና የትግራይ ወጣት ተቀናቃኞች ብቅ እንዳይሉ እየኮረኮሙ እያያችሁ ዬትኛውን የሰላምና የዴሞክራሲ ኮንፈረንስ ነው የምትካፈሉት? ደግነቱ የተካፈሉት ጥቂት መሆናችሁ መልካም ነው።
በመጨረሻ የምለው አንድ ነገር ነው። ኢትዮጵያዊነት ከሁሉም በላይ ነው። 28 ,አመታት ከራሳችን ጎሳ አልፈን ለሌላው እንዳናስብ ተደርጎ የትም አልደረሰንም። እስቲ እኒህን ቅን ሰውዬ ልብ ብላችሁ ተመልከቱ። ሀሜቱንም ሁሉ ሰምተናል። በጭራሽ አለመሆኑን የምታውቁት ከውስጥ የውስጥ ባላጋራ እንኳ ታኮ ሆኖባቸው ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በዝምታ ብዙ ዋጋ የከፈሉ ናቸው ዶር አቢይ። ሌላው ሳላደንቀው የማላልፈው የአቶ ደመቀ መኮንን ጽናትና ብቃት ነው። በጣም አስገራሚ ጽኑ መንፈስ ያላቸው ትልቅ ሰውዬ ናቸው። እንደኔ ምኞት ቢሆን ዶር ብርሀኑ ነጋ፣ ዶር ኦባንግ ሜቶ ከብልጽግናው ፓርቲ ቢቀላቀሉ አገራችን ታላቅ እርምጃ ትሄዳለች ብዬ አስባለሁ። እናንተ የህዝበ ቁጥራችሁን ከፍታ አይታችሁ ልባችሁ በእብሪት ለተወጠረ አክራርያን የአዲሱ አመት ምኞቴ ወደስልጣን መንበሩ እንዳትደርሱ ከልብ እመኛለሁ። ይልቅ የሚያምርባችሁ የምታከሩበትን የተነደፈ ፖሊሲ ይዛችሁ፣ ሰው ሰው የሚሸት ተጻራሪ ፓርቲ በግንባር ፈጥራችሁ አዲሱን ብልጽግና ወይም ሌሎችን በሀሳብ ሞግቱ። ለሀሳብ ሙገታው ደግሞ ካልሆነላችሁ ከላይ እንዳልኩት እርስ በርስ እየተመራረጣችሁ ተጫረሱ። ከህዝቡ ጫንቃ ላይ ግን ውረዱ። አላማረባችሁም። ይህው ነው። ድከም ቢለኝ እንጂ ትሰሙኛላችሁ እንኳ ብዬ እራሴን አላጃጅልም። የበአል ምኞቴ ስለሆነ በአክብሮት ይድረሳችሁ።
መልካም ገናና የፈረንጆች አዲስ አመት!
ተጨማሪ ያንብቡ:  የቀጣዩ መንግሥታችን ሸክም (ይሄይስ አእምሮ)

10 Comments

  1. እግዚአብሔር ይባርክህ ! አንጀቴን ሣይሆን ኢትዮጵያዬን ያመኛል መፍትሄው እንዳንተ ያለ ሀገር ወዳድ ነው ። ይህን የምለው ከአርባ ሠባት ዓመት ስደት የተማርኩት ” ሀገር የለሽ ” ስደተኛ ምን ማለት እንደሆነ ስለተገነዘብኩ ነው ። ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

  2. Did TPLF do all those crimes against humanity alone?? Weren’t all those now puffing up as “yelewuT hawariya” just those actually doing the dirty jobs for Woyane? And the big question of all: what structural change did they bring, except changing their party’s name and their power positions? How many members of OPDO have yet been brought to justice for the glaring crimes they committed in the open?
    And most importantly, since when have you been hired as Abiy’s propagandist?
    You think that all those who oppose your version of “etiopiyawinet” (a cover for Amhara hegemony) and want true federation and genuine democracy, are not Ethiopians??
    Dadhabaa!

  3. “መልካም ሠይፈ ነበልባል” የሚባለውን የአቤ ጉበኛን መፅሐፍ ብታነብ ጥሩ ነበር ። ካነበብኩት ብዙ ጊዜ ቢያልፍም ልጠቅስልህ የምፈልገው በውስጡ ” አህያ አህያን ሲነዳ ተያይዞ ገደል ይገባል ” የሚለውን ነው ። ይህ መፅሐፍ የታተመው በኃይለ ሥላሤ ጊዜ ነበር ። በአሁኑ ሃያ አንደኛ ክፍለ ዘመን እንደ አህያ የሚያስቡም ሆነ የሚነዱ ኢትዮጵያዊ ግለሰቦች ይኖራሉ ብዬ አልገምትም ነበር ። አንዳዶቹን ፅሑፎች ሳነብ ግን ምን ያህል የዋህ ሆኜ መቅረቴን ተገነዘብኩ ። ከጭለማ በፍፁም አልወጣንም ጭላንጭሉም አልታየንም ! ያሣዝናል

  4. ዬ አባጫላ!
    ካኑምቢራሌ ዲ’ሲቲ ናሚቻ ሉቡ ባቃላ ወጊፍ ዳ’ባቴ አያኑማ ዖሮሞፍ ጄታኒሌ ሳፉ ሂንቤክታኒ? ዋራ ኦህዴድ ኬቻ ናሙምቲ አካ አቢይ ሳሙፍ ሉቡ ቃቡ ጂራ? ላማ ኦፊቲ ማጣንሱን ፣ አቢይ ኦፊራፋጌሱን ቱን አማ ዱ’ጋ ላማቱ ባሪ ኦጋ ኢሲኒቲ ጃላቴ ሳኒ ኢሲኒፍ ዳ’ባቴሞ ኢሲኒራዳ’ባቴ? ሜ ናንዱ’ቢሲን አቤ! ሁንዳሺ ዳ’ጌኜራ። አኒ ቆሳ ዋራ ዋያኔ ጃላካቱራ ዲ’ማ ሂንቃቡ ጃሪቲ ሀራስ ቢያአባኮራ ቴቼ ፋግዱ ዲ’ሴ። ዳዳ’ባን አና? ናንኮፋልቺሲን አቤ!!!

  5. አባጫላ የቆጨኝ ነገር
    ድንገት ዖሮሚፋውን በግእዝ ሆሄ ግራ ከገባህ በአማርኛ ልተርጉምልህ። የሚያኮራ የኢትዮጵያ ፊደል እያለ በእንግሊፋ አልመልስልህም መቼስ። እዚህም ላይ ነው አንተንና መሰል አክራርያን ግራ ገብቷችሁ ሰውን ግራ የምታጋቡ። እንግሊዘኛው ሆነ አማርኛው ለናንተ እንደምትሉት ባእድ የኮሎኒያሊስቶች ልሳን ከሆነ ለምን በጻፍኩት አትመልስም ነበር? ምን ልዩነት አላቸው ለናንተ? ወይስ ከኮሎኒያሊስት ልሳኖችም ለፈረንጆቹ ማድላትህ ነው? ካንተ አይነቱ ወገን መሳይ አክራሪ የለየላቸው የጽልመት ውላጆች ሳይሻሉ አይቀሩም። ማ እንደሆኑ አውቀን የምሳቸውን እንሰጣለንና። እንደውም እነሱኑ ትሆን እንዴ እያልኩ እጠረጥራለሁ። እስቲ አቢይ ለዖሮሞ ጠላት ነው ወይም በጎ አያስብም ብሎ የሚያስብ ዖሮሞ በዛሬ ዘመን ለማሰብ በጣም ይከብዳል። አዎ አቢይ ከኦህዴድ የበቀለ ግን ፍጹም ኢትዮጵያዊ የሆነ ብቁና መልካም ሰው ነው። ብዙ የኢትዮጵያ ተከራካሪዎችም አሉ በኦህዴድ ውስጥ። ከዖነግም እንዲሁ ቁጥራቸው ይነስ እንጂ። ለአቢይ ፕሮፖጋንዲስት መሆን ለኢትዮጵያ እንደሆንኩ በክብር እቀበለዋለሁ እስከ ድክመቱ። እንዳንተ የወያኔ ጽልመት ውላጆች ፕሮፖጋንዲስት ልሁንልህ ታድያ? ለማንኛውም ይህው ትርጉሙ፣ ግራ የገባህ ዲጂታል። ድንገት በስህተት አይምሯችሁ ያስብ ይሆን ከማለት እንጂ ከዝንብ ቀፎ ማር ጠብቄ አልነበረም።

    ” አባጫላ ሌላው ቢቀር የበቀለ ወጊን ነፍስ ሊታደግ የራሱን ነፍስ የማገደ አቢይ በመሆኑ ፣ ይህን እንኳ አይታችሁ አታፍሩም በዖሮሞ እምላክ? ከኦህዴድ ባለሟሎች እንደ አቢይ መልካም አይምሮና ልብ ያለው አለ? ለማን ወደራሳችሁ ማስጠጋትና አቢይን ማራቅ እውነት ዘመኑ በከፋባችሁ ጊዜ ለማ ነው የቆመላችሁ ወይስ የቆመባችሁ? ሁሏን ሰምተናል እባክህ አታናግረኝ። እኔ ጥሌ ከጃንጥላ ያዦች ሳይሆን ከዋንኞቹ በአገሬ ላይ አሁንም ጤና ከሚነሱን የጽልመት ውላጆች ወያኔዎች ነው። ደካማ ብለህ ባታስቀኝስ?”

  6. Ethiopia has never been just one ethnic group. Ethiopia has no majority religion sect even, let alone majority ethnic group. But Ethiopia was the only country in Africa who kept her independence. Ethiopia doesn’t have any independence day.

    The best solution and probably the only solution is to find a way to live in peace and harmony TODAY.

    Every gov’t that came in started with telling Ethiopians how bad the previous gov’t was; in a way telling people they should be grateful and OBEY. But what made ABIY AHMED very different was he confessed that he was bad for being part of ethnic apartheid that tortured citizens in dark cells.

    And sure Prof. Berhanu Nega had left an impression and Dr. Abiy is a result of all that struggle. He is Ethiopian and has no problem appreciating what other leaders of Ethiopia has done before him.

    Abiy’s greatest challenge came from a certain group that hated him because he is Oromo like them. Some of them who are now giving his administration a head ache were making speeches to the crowd Dr. Berhanu and Tamagn gathered in D.C. swearing they were more Ethiopians just a decade ago.

    TPLF is TPLF and Abiy is offering them amnesty and they are not taking it. They are sabotaging Eritrean and Ethiopian new peace deal. By now we should’ve been visiting Asmara and Massawa and Assab should have been the port but TPLF is financing mosque burnings now because burning churches didn’t bring the result they wanted.

  7. “Warra ‘Ohdid’ keecha namumti akka Abiyy sammuu fi lubbuu qabu jiraa?” No! He is supposed to be the ‘best’, biyya warra jaamaatti kan ija tokko qabu mootii dha, akkuma jedhamu. Since he is the best, the country is therefore reeling from one chaos to the next, like a ruderless boat. He and the likes of you point your fingers to some imaginary powerful enemy causing all the conflicts, whereas the true reason is that Abiy is incapable of acting like a leader in times of difficulty. Instead he spends his time filing at his own image building, while elements in the state security apparatus are destabilising the country. Like his predecessor HM, the Neftegna advisors and secret agents he surrounded himself with feed him false information and mislead him. If Ethiopia is going to be “saved” in this way, you are going for a surprise! From whom are you thinking of saving Ethiopia from?? From the people who want to be owners of their country, and thus install a dictator?
    He didn’t save Bekele Wagi from the being murdered. He only announced the killing beforehand! Why was he serving in the 1st place an intelligence service that has the massacre of all concious Oromos and TPLF’s opponents as its highest priority??? Indewuleta liqoTerlet?? Too pathetic!!
    Jaamtota nam-tokko waaqeffattan, rakkoon biyyaa eessaan isiniif gala? Hamma namaa hin geessu, cabsa namaa hin teessu!

  8. To know what your version of ‘etiyopiyawinet’ to Oromos, see the interview of Kuwee Kumsaa on LTV, and what Abiy’s ‘Meddemer’ has in store for us, listen to Colonel Gammachuu Ayyaanaa on ONN. Colonel Gammachuu came back from Eritrea to struggle for Oromo right peacefully, but he was abducted by Abiy’s secret agents and kept in prison for 11 months in the same way TPLF used to treat Oromo prisoners. He was not alone. There are thousands of Oromos languishing in official and secret prisons still today. Where is the change for the Oromo?? That is how you brag “etiyopiyawinet yashenfal!”. Give us a break!!

  9. አባ ዊርቱ
    ወደድክም ጠላህም በመጀመሪያ እግዚአብሔር እኔን ኦሮሞ አድርጎ ነዉ የፈጠረኝ፤ በዘሬ ማለት ነዉ። ኢትዮጲኣዊነቴን ግን “ነህ” ተብዬ ነዉ እንጂ እግዚአብሔር የሰጠኝ አይደለም። ሌላዉ የጫነብኝን ማንነት ባልፈልገዉ መጣል እችላለሁ። ኦሮሞነቴን ግን መጣል አልችልም። ገባህ አንተ ፍናፍንት?

Comments are closed.

Share