መድረክ መነቃነቅ ጀመረ

በዘሪሁን ሙሉጌታ

የስድስት ፓርቲዎች ግንባር የሆነው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በሀገሪቱ የፖለቲካ እንቅሰቃሴ ፈጠን ወዳለ እንቅስቃሴ ለመግባት መዋቅሮቹን ማነቃነቅ ጀመረ።

የግንባሩ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ባለፈው ሰኞ ባካሄዱት ስብሰባ የግንባሩ አራት የተግባር ኮሚቴ አባላት የመዋቅር ለውጥ በማድረግ የራሳቸውን ዝርዝር እቅድ ይዘው እንዲቀርቡ አዟል።

ለግንባሩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት የግንባሩ አራት የተግባር ኮሚቴዎች በስራቸው ንዑስ የስራ ኮሚቴዎችን በማዋቀር፣ በዋና ጽ/ቤቱም ቋሚ ባለሙያዎችን በመቅጠር ጭምር የግንባሩን የጽ/ቤት የእለት ተዕለት ስራ ለማከናወን ወስኗል።

ግንባሩ ከአንድ ወር በፊት ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ በኋላ በአባል ፓርቲዎች መካከል ያለው የመተማመን ደረጃ እየተሻሻለ በመምጣቱ ስራዎችን በጋራ የማንቀሳቀስ ሁኔታ ተጀምሯል። በመጪው አርብ በድጋሚ በሚካሄደው ተጨማሪ ስብሰባ የግንባሩን ስራ ይበልጥ ለማቀናጀት የሚያስችሉ ልዩ ልዩ እቅዶች እንደሚቀርቡ ተገልጿል።

ግንባሩ በቅርቡ የራሱን ድረገጽ መክፈቱ እንዲሁም ልሳን የማዘጋጀቱንም ተግባር ልዩ ትኩረት መስጠቱ እንዲሁም ግንባሩን ለማጠናከር የሚያስችሉ ሰፋ ያሉ የገንዘብ ማሰባሰብ እንቅስቃሴዎች ላይ እንደሚሰማሩም ምንጫችን ጠቁሟል።

ቀደም ሲል ‘‘መድረክ ተኝቷል’’ የሚል ወቀሳ ከአንዳንድ የፓርቲው አመራር አባላት በግልፅ ትችት ሲቀርብበት ቆይቷል። በግንባሩ ውስጥ ሥራውን በተግባርና በአመለካከት ደረጃ የሚያጓትት አካል እንዳለም ምንጫችን ያመለከተ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግንባሩ ወደ ስራ ሲገባም ስራውን የሚያጓትተው እና የሚያፋጥነው አካል እንደሚለይም ታውቋል።

መድረክ ከሁለት አመት በኋላ የሚካሄደው የ2007 ሀገር አቀፍ ምርጫ ዋናው ግቡ መሆኑን የጠቀሰው ምንጫችን በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ውስጥ በስድስቱ ፓርቲዎች መካከል በሚፈጠረው የጋራ መግባባት ከግንባር እስከ ውህደት ሊደርስ የሚችልባቸውን አማራጮች እንደሚፈትሽ የጠቆመ ሲሆን ግንባሩ አሁን እየፈጠረ ባለው አዲስ መዋቅር አዳዲስ ጠንካራ ሰዎች ይፈጠራሉ የሚል ተስፋ ይዟል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሸንጎ መግለጫ አወጣ | "ሀላፊነት እወስዳለሁ ማለትና ይቅርታ በተግባር መተርጎም አለበት"

ግንባሩ ከፍተኛ የበጀት እጥረት እንዳለበት ተደጋግሞ ቢገልፅም፤ የበጀት እጥረቱ መድረኩ ስለስራ ያጋጠመ ችግር መሆኑም የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። በቀጣይ ሳምንታትም ግንባሩ ያዘጋጀው ማኒፌስቶ በመገናኛ ብዙኋን እና በዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ይፋ እንደሚደረግም ምንጫችን ጠቁሟል።

በአሁኑ ወቅት ስድስት ፓርቲዎች በግንባር ያዋቀረው መድረክ በ2002ቱ ምርጫ ከኢህአዴግ በመቀጠል ብዙ መራጭ ማግኘቱ አይዘነጋም።n

Source: Sendek Newspaper

5 Comments

  1. As long as Beyene Petros, Merrara gudina and the like are within Medrek, this group will go no where. In the last 15 years, merrara gidina, beyene petros and those like them have been sabotaging the struggle of the people for freedom, democracy and justice. the are happy to be called’ loyal opposition’ , which is a name given to them by the ethno-fascist woyane junta.

    medrek should remove this internal ‘implants’ and elect new leaders and redefine its objective. The organisation is fully penetrated by woyane cadres from top to bottom that are eating away at the organisation like a cancer. the cancerous woyane disease must be purged out of the organisation and measures taken to prevent the woyane infesting the organisation in the future.

  2. Negasso gidada does not even believe that Meles as leader of Tigre people liberation front is a narrow nationalist and ethno-fascist whose main pleasure in life was inciting inter ethnic and religious violence, genocide and ethnic cleansing. How can such a man be the leader of an opposition party when he does not want to accept that this is where the struggle should focus on, ie opposing fascism, ethnicism , genocide and ethnic cleansing. If NEGASSO DOES NOT ACCEPT THAT MELES AND HIS CADRES ARE THE CAUSE OF ALL EVIL, who is he opposing.

    Ethnic cleansing AND GENOCIDE of gambellans, amharas, ogadenis, is continuing apace by TPLF. Has Medrek said a word on this issue so far. NO THING! BECAUSE Negasso does not want to upset TPLF.

  3. What is amazing is their name is hidden now because they don’t want to be called ethnic organization, they never say anything when Amharas, Gambellas, Muslims are persecuated. They will never do anything for Ethiopian people, they are old indirect supporter of tplf. Most of them are cheating the Oromo people by sticking Oromo name tag. Shame, Shame

  4. These are all Ethnic politicians they do not represent the whole Ethiopia. We know they are seven groups but all of them are almost the same ideology with Tigray People Libration Front. No change, Ethiopia need inclusive parties not MEDREK

Comments are closed.

Share