February 26, 2019
2 mins read

የጄ/ል ክንፈ ወንድም የሆኑት አቶ ኢሳያስ ዳኘው ለቀረበባቸው ክስ መቃወሚያቸውን አሰሙ

94285

የጄ/ል ክንፈ ወንድም የሆኑት አቶ ኢሳያስ ዳኘው ለቀረበባቸው ክስ መቃወሚያቸውን አሰሙ፡፡ ተጠርጣሪው የኢትዮ ቴሌኮም ሀላፊ ሆነው በሚሰሩበት ወቅት ዜድቲኢ ከተሰኘው የቻይና ኩባንያ ጋር በፈፀሙት ውል መከሰሳቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=14ql5rq_pMI

አቃቤ ህግ ባቀረበባቸው በዚህ ክስ ከዜድቲኢ ጋር 44‚ 510‚ 971.00 (አርባ አራት ሚሊዩን አምስት መቶ አስር ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባ አንድ) የአሜሪካን ዶላር የግዥ ውል ለጊዜው ስማቸው በክሱ ውስጥ ካልተጠቀሱት ግለሰቦች ጋር ቀጥታ ግዥ እንዲፈጸም ማድረጋቸው ተገልፆ ነበር፡፡ በግዢውም በስውር ጥቅም በመመሳጠር በመንግሥትና በኮርፖሬሽኑ የተሰጣቸውን ሹመት፣ ሥልጣን ወይም ኃላፊነት በግልጽ ተግባር ወይም በግድፈት ያላግባብ በመገልገል እንዲሁም ከተሰጣቸው ሥልጣን በላይ አልፎ በመስራት የማይገባውን ጥቅም ለማግኘት እንዲሁም ለዜድ.ቲ.ኢ. ለማስገኘት በማሰብ በመንግሥትና በኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬሽን ጥቅም ላይ ጉዳት የማድረግ የማድረግ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው ነበር፡፡ ጉዳዩን ሲመለከተው የነበረው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሹ ያላቸውን የክስ መቃወሚያ ይዘው እንዲቀርቡ ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቷቸው የነበረ ሲሆን የተከሳሽ ጠበቆችም የክስ መቃወሚያቸውን ዛሬ ለፍርድ ቤቱ አቅርበዋል፡፡ የግራ ቀኙን ክርክር የተመለከተው ችሎቱም ዐቃቤ ህግ ለቀረበው የክስ መቃወሚያው መልስ እንዲሰጥ ለማድረግ መጪው አርብ የካቲት 22 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡

94282
Previous Story

ምስክሮችን ፎቶ በማንሳት ተጠርጥረው የታሰሩት ዋስትና ተፈቀደላቸው

doing business
Next Story

ንግድን የማሳለጥ (Doing Business) መርሐ ግብር የአንድ ወር አፈጻጸም ግምገማ በጠ/ሚር ጽ/ቤት ሲካሄድ ውሏል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop