የፌዴራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ዛሬ በዋለው ችሎት ፎቶ በማንሳት በማህበራዊ ድረ ገጽ ሲለጥፉ በቁጥጥር ስር ውለዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎች የጠየቁትን የዋስትና ጥያቄ ተቀበለ።
https://www.youtube.com/watch?v=14ql5rq_pMI
መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በምርመራ ላይ በሚገኙ ግለሰቦች ላይ ምስክርነት በመስጠት ፍርድ ቤት ቅድመ ምርመራ ላይ እያሉ፥ ፎቷቸውን በማንሳት በማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ በመለጠፍ መጠርጠራቸውን ተከትሎ ሲያደርግ የቆየውን ምርመራ ማጠናቀቁን እና የምርመራ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ ማስረከቡን ለችሎቱ ገልጿል። ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ፍርድ ቤቱ ዋስትና እንዲፈቅድላቸው ባመለከቱት መሰረት በሁለት ሺ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ አዟል፡፡