አፍራን ቀሎ የሙዚቃ ቡድን በሚሊኒየም አዳራሽ ታሪካዊ የተባለውን የሙዚቃ ኮንሰርቱን አቀረበ

በኢትዮጵያ የኦሮሚኛ የሙዚቃ ውስጥ ትልቅ ሥፍራ ያለው አፍራን ቀሎ የሙዚቃ ቡድን በዛሬው ዕለት በሚሊኒየም አዳራሽ ታሪካዊ የተባለውን የሙዚቃ ኮንሰርቱን አቀረበ::

https://www.youtube.com/watch?v=p8iBU5RCUVc&t=50s

በስደት ቆይቶ ወደ ሃገሩ ከሁለት ሳምንት በፊት የተመለሰው ይኸው የሙዚቃ ቡድን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ሚሊኒየም የሙዚቃ ኮንሰርቱን ሲያቀርብ በርካታ አድናቂዎቻቸው እና የተለያዩ ፖለቲከኞችና ታዋቂ ሰዎች በክብር እንግድነት ተገኝተዋል:: የአፍራን ቀሎ የሙዚቃ ቡድን በሃገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች እየተዘዋወሩ የሙዚቃ ሥራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ሰምተናል::

አፍራን ቀሎ ባንድ በ1960ዎቹ ውስጥ በድሬደዋ ከተማ እንደተመሰረተ የተጻፉ ታሪኮች ያስረዳሉ::

ተጨማሪ ያንብቡ:  የድምጻዊ ሸዋንዳኝ ኃይሉ አዲስ አልበም እየተጠበቀ ነው
Share