January 24, 2019
3 mins read

ድሬዳዋ ዛሬ በጎማ ጭስ ስትታጠን ዋለች

93805

በዛሬው እለት ከጠዋቱ አራት ሰአት ጀምሮ በድሬደዋ ከፍተኛ ተቃውሞ ተደርጓል፡፡ ከንቲባው ያነጋግሩን ያሉ ወጣቶች መንገድ ዘግተው ጎማ በማቃጠል ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ የዋሉ ሲሆን በፖሊስ ላይም ድንጋይ ወርውረዋል፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=pJpzsue5H3c&t=917s

ተቃውሞው ከፍተኛ ደረጃ ሲደርስ መከላከያ ገብቶ የማረጋጋት ስራ መስራቱን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡ የተቃውሞው መነሻ በጥምቀት በአል አከባበር ወቅት የተፈጠረው ረብሻ ነው፡፡ የድሬዳዋ ፖሊስ ትላንት ባወጣው መግለጫ በጥምቀት በአል ማግስት ጥር 13 ቀን 2011አ.ም የእግዚአብሔር አብ ታቦትን አስገብተው በሚመለሱ ምእመናኖች ላይ የተወረወረ ድንጋይን ተከትሎ በተፈጠረው ግጭትና ሁከት ተጠያቂ ናቸው ያላቸውን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን መግለፁ ይታወቃል፡፡ፖሊስ 84 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ቢናገርም በዛሬው ተቃውሞ የታሰሩት ይፈቱ የሚል መፈክርም ተሰምቷል፡፡

በተጨማሪም በከተማው ውስጥ ከፍተኛ የነዳጅ እጥረት ስላለ አስተዳደሩ መፍትሄ እንዲሰጥም ተጠይቋል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከፍተኛ የስራ አጥነት በመኖሩ የሚመለከተው አካል በተለይም ከንቲባው በዚህ ዙሪያ እንዲሰሩ ወጣቶቹ ጠይቀዋል፡:

የድሬደዋ ፖሊስ ኮሚሽን አስተማማኝ ሰላም ለማስፈንና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየሰራሁ ነው ብሏል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ሳጅን ባንተአለም ግርማ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ጥር 12/2011 ፖሊስ የችግሩ ቀስቃሾች ናቸው ብሎ የጠረጠራቸውን ሰዎች በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያካሄደ ነው፡፡
በተጠርጣሪዎች ላይ መረጃና ማስረጃ አሰባስቦ ለፍርድ ለማቅረብ  የተቀናጀ ሥራ ይከናወናል ብለዋል፡፡
ግጭቱ ከየትኛውም ብሔር ሆነ እምነት ጋር ግንኙነት እንደሌለው ኃላፊው ተናግረዋል።
አንድ መድኃኒት ቤት በከፊል ቃጠሎ እንደደረሰበትም አስታውቀዋል፡፡
በአስተዳደሩ የሕዝቡን ሰላም ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ ፖሊስና የፀጥታ አካላት ተቀናጅተው እርምጃ እንደሚወስዱ ዋና ሳጂን ባንተዓለም  ገልጸዋል፡፡
ኅብረተሰቡም የሕግ የበላይነትን ለማስከበር የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንዲያጎለብት  ጠይቀዋል።

john legrand zhO4JJv0zi4 unsplash
Previous Story

Best ways to cook beefs

93808
Next Story

መንግስትና ኦነግ ተኩስ ለማቆም ተስማሙ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop