January 12, 2019
2 mins read

ለቀናት ታግተው የተለቀቁት የደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንት ‹‹እኔ ፖለቲካ አይመለከተኝም፣ ያገቱኝ ሰዎችም የተሳሳቱ ይመስለኛል›› አሉ

93697

ለቀናት ታግተው የተለቀቁት የደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንቱ ዶ/ር ደላሳ ቡልቻ ‹‹እኔ ፖለቲካ አይመለከተኝም፣ ያገቱኝ ሰዎችም የተሳሳቱ ይመስለኛል›› አሉ::
https://www.youtube.com/watch?v=G6LalCqO72M

ዛሬ በአዲስ አበባ ለንባብ ከበቃው ሸገር ታይምስ መፅሄት ጋር ቃለምልልስ ያደረጉት ዶ/ር ደላሳ ቡልቻ በታገቱበት ወቅት ምንም የደረሰባቸው አካላዊም ሆነ ስነልቦናዊ ጥቃት እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ ይሁንና የማያውቁት ነገር ስለገጠማቸው እንደከበዳቸው አስረድተዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹ወታደር ብሆን የገጠመኝ ምንም ላይመስለኝ ይችላል፡፡ እኛ ከቢሮ ውጭ ምንም አናውቅም፡፡›› ብለዋል፡፡ የሙያ ሰው እንጂ ፖለቲከኛ አለመሆናቸውን ገልፀውም የታገቱበት ምክንያት ግራ እንደሆነባቸው ጠቁመዋል፡፡ በቃለምልልሱ ‹‹እኔ ስለተማሪ ሽሮና ጤንነት እንጂ ስለፖለቲካ የማይመለከተኝ ሰው ነኝ፡፡›› ያሉት ዶ/ር ደላሳ ጨምረውም ‹‹ስለተማሪው ደህንነት እንዲሁም ስለትምህርት ጥራት ቀኑን ሙሉ የሚያወራና እሱንም ማድረስ የማይችል ሰውን እንዲህ ማድረግ አይገባም፡፡ ከእንደዚህ አይነት ሰውም ምንም አታገኝም፡፡ በዚህ ጉዳይ እነሱም የተሳሳቱ ይመስለኛል›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ዶክተሩ ለቀናት ታግተው የተለቀቁ ሲሆን ለእገታው ሃላፊነቱን የወሰደ አካል እስካሁን የለም፡፡

1 Comment

Comments are closed.

93694
Previous Story

በኢትዮጵያ የሚገኘው የናይጄሪያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ ዜጎቹ ማስጠንቀቅያ ሰጠ

Next Story

አትሌት ደራርቱ ቱሉ በአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን አከባቢውን በመወከል የቦርድ አባል ሆና ተመረጠች

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop