ሕወሃት ለሁለት በተከፋፈለበት ወቅት በአቶ መለስ ዜናዊ ከመከላከያው ኢታማዦር ሹመነታቸው የተባረሩት ጀነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ “በአማራ ልሂቃን የሚነሳው የህገ መንግስት ተቃውሞ መሰረተ-ቢስ ነው ፤ ህገ-መንግስቱ ሲፀድቅ ህዝብ ተሳትፎበታል ፤ እንደውም በየጣብያው ምን ያህል ህዝብ እንደተወያየበት ሁሉ ስታቲክስ ከዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጋር ነበር” ሲሉ ከዋልታ ቴሌቭዥን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ተናገሩ::
https://www.youtube.com/watch?v=aVUdalQQ5Mk&t=54s
“አሁን እየሆነ ያለው በለውጥ ስም ጥላቻ ነው እየተንጸባረቀ ያለው ይህ መሆን አልነበረበትም ፤ ምክንያቱም አሁን እየገዛ ያለ ሃይል ግልጽ የሆነ የመዳረሻ ፍኖተ ካርታ የለውም ፤ ይህ ትልቁ ችግር ነው። በቅርብ ግልጽ የሆነ ሁሉኑም ያሳተፈ ሀገራዊ ፍኖተ ካርታ መውጣት አለበት።” ያሉት ጀነራሉ “ዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን ሲመጣ ከማንም በላይ የትግራይ ህዝብ ነበር ደስተኛ የሆነው ፤ “ባልበላሁት ባልጠጣሁት የምወቀስበት ምክንያት ከንግዲህ አይኖርም ፤ አሁን ነጻ ወጥቻለሁ” ነበር ያለው። ነገር ግን ቀስ በቀስ የትግራይን ህዝብ አንገት የሚያስደፉ ንግግሮች ተጀመሩ ፤ የትግራይ ህዝብ ብበአዴን ሰዎች አካኪ-ዘራፍ ሲባልበት ፌደራል መንግስት ዝም አለ፤ በትግሉ፣ በላቡ የተሰራ መንገድ ሲዘጋም ፌደራል መንግስት ዝም አለ ፤ የግሌ አቋም ይቅር፣ ህዝቡ ግን ትክክል አይደለም ብየ አላስብም።” ብለዋል::
በአማራና በትግራይ ክልሎች አዋሰኝ አካባቢዎች የሚነሱ ግጭቶች መንስዔ በ1984 ዓ.ም የተደረገው ህዝብን ያላማከለ አከላለል እንደሆነ የአዴፓ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ደሴ ጥላሁን ለጀርመን ድምጽ ሲናገሩ ሰምተናል::